‹የክርስቶስ አንዲት በግ መከራን ስትቀበል ከማይ እኔ የበጉ እረኛ መከራ መቀበልን እመርጣለሁ›
ይህንን የተናገረው ዮሐንስ አፈወርቅ ነበር፡፡ የቁስጥንጥንያዋ ንግሥት አውዶቅስያ የአንዲት ክርስቲያን ምእመንን መሬት ወስዳ
ባሰቃየቻት ጊዜ ለተግሣጽ የተናገረው ነው፡፡ እንዳለው አልቀረም አውዶቅስያ ባደረሰችበት መከራ ተግዞ በዚያው ሞትን ተቀብሏል፡፡
እውነተኛ አባት ስለ በጎቹ ራሱን አሳልፎ ይሰጣል እንጂ በጎቹን ለራሱ ክብርና ጥቅም ሲል አሳልፎ አይሰጥም፡፡ ፓትርያርክ ማለት
በግሪክ ‹ታላቅ አባት› ማለት ነው፡፡ የታላቅ አባት ተግባር የልጆቹን ሥራ ማፍረስ አይደለም፤ ለዚህማ አባት አያስፈልግም ሰይጣን
እንጂ፤ የታላቅ አባት ሥራ ልጆቹን መክሰስ አይደለም፤ ለዚህማ ሰይጣን እንጂ አባት አያስፈልግም፡፤ የታላቅ አባት ሥራ ልጆቹን ጠርቶ
መውቀስ እንጂ በር መዝጋት አይደለም፤ ለዚህማ አባት አያስፈልግም ሰይጣን እንጂ፡፡ የታላቅ አባት ሥራ ልጆቹን ማቀፍ እንጂ ማባረር
አይደለም፤ ለዚህማ ሰይጣን አለ፡፡
ፓትርያርኩ እንጨት የሚሸጡ እናቶች ካወጡት የእንጦጦ ኪዳነ ምሕረት ገንዘብ ግማሽ ሚሊዮን ብር እንደዋዛ በአንድ ሙሰኛ ሲነጠቅ
ተኝተዋል፤ በመሐል ከተማ በሚገኙ አብያተ ክርስቲያናት የተሠሩ ሕንጻዎች በጎጆ ቤት ዋጋ በሙስና ለዐሠርት ዓመታት ሲከራዩ ተኝተዋል፤
ከመንበረ ፕትርክናቸው ሥር ባለች አጥቢያ የቤተ ክርስቲንን ገንዘብ አናስበላም ያሉ ካህናትና ምእመናን ሲባረሩ ተኝተዋል፡፡ በሕዝብ
ጥያቄ ሽፋን ጽንፈኛ አቋምን በሚያራምዱ ሰዎች አብያተ ክርስቲያናት ሲቃጠሉ ይተኛሉ፤ የስልጤ ዞን ምእመናን በሃይማኖታችን ምክንያት
መከራ እየተቀበልን ነው ሲሉ ይተኛሉ፤ ቤተ ክህነቱ የኑፋቄ ማኅደር ሲሆን ይተኛሉ፤ የገጠር አብያተ ክርስቲያናት ሲዘጉ፣ ገዳማትና
አድባራት ሲፈርሱ፣ የአብነት ትምህርት ቤቶች ሲበተኑ ይተኛሉ፤ በመሥዋዕትነት የተመሠረቱት የደቡብ አፍሪካ አብያት ክርስቲያናት በሙሰኛ
አመራሮች አደጋ ላይ ሲወድቁ ይተኛሉ፣ ይሄ ሁሉ ዘለፋና ኑፋቄ በቤተ ክርስቲያን ላይ ሲዘንብ ይተኛሉ፡፡
መናፍቃንን የሚተች ጽሑፍ በኦርቶዶሳውያን ተጻፈ ሲሏቸው፤ ምእመናንን የሚያጸና ጉባኤ ሊዘጋጅ ነው ሲሏቸው፤ ሕዝቡ ወደ ቤተ
ክርስቲያን እየመጣ ነው ሲሏቸው፤ ወጣቱ ትውልድ ቤተ ክርስቲያኑን ለማገልገል እየተጋ ነው ሲሏቸው፤ ዲያስጶራው ሕዝብ በእናት ቤተ
ክርስቲያን ሥር ሆነ ሲሏቸው፤ ቤተ ክርስቲያንን የሚገልጥ ዐውደ ርእይ ሊዘጋጅ ነው ሲሏቸው፤ መንፈሳዊ የቴሌቭዥን ፕሮግራም ሊቀርብ
ነው ሲሏቸው ያን ጊዜ ብዕራቸውን ይዘው ለማገድና ለመክሰስ ይነቃሉ፡፡ አባ ጊዮርጊስ ዘጋሥጫ ‹ድንግል ሆይ የአንቺን ምስጋና ለመጻፍ
ምንጊዜም ብእሬ ቀለም እንደያዘ ነው› ነበር ያለው፡፡ የፓትርያርኩ ብእር ግን ምእመናንን የሚያጽናና ጦማር ለመጻፍ ወይም ድንግልን
የሚያመሰግን ድርሳን ለመድረስ የሚጨበጥ አይደለም፡፡ እንደ ጠንቋይ ብዕር ለማፍዘዝና ለማደንገዝ እንጂ፡፡
የፓትርያርክ ዋናው ሥራው የሀገር ደኅንነት እንዲጠበቅ ‹ዕቀብ ሕዝባ ወሠራዊታ ለሀገሪትነ ኢትዮጵያ› እያለ መጸለይ፤ የምእመናን
ድኅነት እንዲረጋገጥም ሃይማኖት ማስተማር፣ በጎችን መሠማራትና ቀኖናን መጠበቅ ነበረ፡፡ ለቅዱስ ጴጥሮስ ‹በጎቼን ጠብቅ፣ አሠማራ›
ነበር የተባለው፡፡ መጠበቅ- ከክህደት፣ ከኑፋቄ፣ ከኃጢአት ከበደል፤ ማሠማራት - በትምህርት፣ በምግባር፣ በትሩፋት፣ በአገልግሎት፣
በጽድቅ መስክ ላይ፡፡
‹ባለሞያ ሴት የሠፋችውን ወራንታ፣ ጅል ትተረትረዋለች› እንደተባለው በደኅና ጊዜ ትጉኃን አበው የሰበሰቧቸውን ወጣቶች ካልበተንኩ
ብሎ እንዴት አንድ ፓትርያርክ ይነሣል፡፡ ወጣቶቹ ሊሳሳቱ፣ ሊያጠፉም ይችላሉ፡፡ ቤተ ክርስቲያኒቱ ግን ለዚህም መንገድ ያላት ቤተ
ክርስቲያን ናት፡፡ የመንግሥት ባለ ሥልጣናት ሳይቀሩ የገዛ ልጆችዎን ያወያዩ ሲሏቸው በራቸውን ጠርቅመው የሚዘጉ ፓትርያርክ በታሪክ
የሚጀመሪያው መሆን አለባቸው፡፡ በሱራፊ ነበልባል የተዘጋች ገነት ስትከፈት በፓትርያርክ የተዘጋች የቤተ ክህነት በር ልትከፈት አልቻለችም፡፡
ሰይጣንን ከእግዚአብሔር ጋር ለማነጋገር የደከሙ እነ ክርስቶስ ሠምራን የመሰሉ ቅዱሳን ባሉባት ቤተ ክርስቲያን እረኛው ከመንጋው
ጋር መነጋገር አቃተው፡፡ ኢየሱሳውያንን በዐደባባይ ሳናነጋግራቸው መሄድ የለባቸውም ብለው የተሟገቱ እነ እጨጌ በትረ ጊዮርጊስ በነበሩባት
ቤተ ክርስቲያን የገዛ ልጆቹን ለማነጋገር በር የሚዘጋ እጨጌ ተፈጠረ፡፡ የመካ ቁራይሾችን አሳልፈን ለጠላቶቻቸው አንሰጥም የሚሉ
አበው በነበሩባት ቤተ ክርስቲያን የገዛ ልጆቹን አሳልፎ የሚሰጥ አባት መጣ፡፡
የኦርየንታል አብያተ ክርስቲያናት በ1972 እኤአ ካይሮ ላይ ባደረጉት ጉባኤ ከተስማሙባቸው ነገሮች አንዱ የኦርቶዶክሳውያን
ጳጳሳት ተልዕኮ ነበረ፡፡ እንዲህ ይላል ‹ኦርቶዶክሳውያን ጳጳሳት አምስት ተልዕኮ አላቸው፡፡ እነዚህም
1. ወንጌልን መስበክ(Preach the Gospel)
2. ምሥጢራተ ቤተ ክርስቲያንን መፈጸም(Administer the Sacraments of the Gospel.)
3. የቤተ ክርስቲያንን እምነት፣ አንድነትና ቀኖና መጠበቅ(Guard the faith, unity, and
discipline of the church.)
4. ለካህናትና ለምእመናን የቅድስና ምሳሌ መሆን(Be a moral example of holiness and
wholesomeness.)
5. በእረኛውና በበጎች መካከል ያለውን ክፍተት ማጠበብ(Diminish the distance between bishops and their
flock.)
ለመሆኑ የእኛ አባት የቱን ነው እየፈጸሙ ያሉት? ወይስ ከኦርየንታል አብያተ ክርስቲያናት ማኅበር ውጭ ሆነናል?
ዐውደ ርእዩ የማይደረግበት በቂ ምክንያት ከነበረ ቢያንስ ከሳምንት በፊት መግለጥ ይቻል ነበር፡፡ ዓላማው ግን ማበሳጨት፣
ዐመጽ ማስነሣት፣ ተሥፋ ማስቆረጥና ምእመናንን ወደማይፈልጉት መሥመር መውሰድ ነው፡፡ ለዚህ ነው ፈያታዊ ዘየማን ገነት በገባባት
ሰዓት ዐውደ ርእዩ እንዲዘጋ የተደረገው፡፡ የዚህች ሀገር ሰላም አይፈለገም? ምእመናን ሀገር እንደሌላቸውና መብት እንደሌላቸው ራሳቸውን
እንዲቆጥሩ ይፈለጋል? ‹ለቀኑ ክፋቱ ይበቃዋል› እንዲል ሀገሪቱ ያለባት ችግር አይበቃትም? ተጨማሪ ችግር ማምረት ይፈለጋል?
ችግሩ ሁሉ እየተፈጠረ ያለው በመንግሥት ስም ነው፡፡ ‹መንግሥት አዞናል፤ እገሌ የተባለ ባለ ሥልጣን ብሎናል፤ ፖሊስ እንጠራለን፤
ደኅንነት እናዛለን› ነው በቤተ ክህነቱ ዘንድ የሚባለው፡፡ እውነት መንግሥት በስሙ የሚሠራውን ያውቀዋል፤ ካወቀውስ ዝም ይላል?
ቤተ ክህነቱ በሚያመጣው ዳፋ መከራ ለመቀበልስ ዝግጁ ነው? ይህ አካሄድስ ለሀገሪቱ ደኅንነት የሚበጅ ነው? ዐውደ ርእዩ እንዲዘጋ
ያዘዘውስ የትኛው መንግሥት ነው? አንዱ የሚፈቅድ ሌላው የሚዘጋ ስንት መንግሥት ነው ያለው? ወይስ ‹ደብዳቤ መጻፉ አላዋጣምና ዝጋልኝ›
ተብሎ እጅ የተሰነዘረለት አካል ያደረገው ነው? መጽሐፉ እንደሚል ‹የማይገለጥ የተሠወረ› አይኖርምና ዐውቀነዋልም፣ እናውቀዋለንም፡፡
የገዛ ፓትርያርካችን ለእኛ ለምእመናን ድኅነትን እንዳናገኝ ሥጋት ሆነውብናል፡፡ የታገሡትን ሁሉ ለክፋት በማነሣሣት ደግሞ
ለሀገሪቱ ደኅንነት ሥጋት እየሆኑ ነው፡፡ የምእመናኑን ሥጋት ሲኖዶሱ፤ የሀገሪቱንም ሥጋት መንግሥቱ ሊያስቡበት ይገባል፡፡ ከቤተ
መቅደስ የተነሣ ችግር መጀመሪያው እንጂ መጨረሻው አይታወቅምና፡፡ እንዲህ ያሉ ነገሮች የምእመኑን የአስተሳሰብ ቅርጽ ይቀይራሉ፡፡
የሐበሻን ሥነ ልቡና ለሚረዳ ደግሞ ሲረገጥ እንደሚጠክር ጭቃ ያጠነክራሉ፡፡ ሲሞረድ እንደሚሳል ቢላዋ፣ ሲቀረጽ እንደሚሾል እርሳስ
ያደርጋሉ፡፡ በዐውደ ርእዩ የሚማሩት የሚያዩት ብቻ ነበሩ፡፡ አሁን ግን ያላዩትም እንዲማሩ አድርገዋል፡፡ ሐሳብና ርእዮት ሊያስተባብረው
የማይችለውን ተጠቂነት ያስተባብረዋል፡፡ ተጠቂነት ክርክርና ውይይት፣ ማስረጃና መረጃ አይጠይቅም፡፡ መጠቃቱን ያወቀ ሁሉ ራሱ ገብቶት
ይተባበራልና፡፡ ምናልባትም ምእመናንን ከገድል ተራኪነት ወደ ገድል ሠሪነት ያሻግራቸው ይሆናል፡፡ ‹እዚያም ቤት እሳት አለ› አሉ
አለቃ፡፡
እንደ ሶምሶን ከአንበሳ ሬሳ ማር ለማውጣት ግን በሳል አመራር ይጠይቃል፡፡ የማኅበሩ አመራርም ቢሆን ጊዜውን አይቶ የሚሣለጥ
አመራር እንጂ የተቸከለ አመራር መሆን የለበትም፡፡ የፓትርያርክ ማትያስ ዘመን እንደ ፓትርያርክ ጳውሎስ፣ የጠቅላይ ሚኒስትር ኃይለ
ማርያምም ዘመን እንደ ጠቅላይ ሚኒስትር መለስ አይደለም፡፡ አሁን የሆነው ነገር ሊሆን እንደሚችል ቀድሞ እየታወቀ ከግንቡ ጋር እስኪጋጩ
ድረስ ቆሞ መጠበቅ ብልህነት አይደለም፡፡ አሁንም ‹እገሌ የተባለ ባለሥልጣንን አናግረናል፤ እገሌ የተባሉ አባት አይዟችሁ ብለውናል›
እያሉ መጓዝ የሚያዋጣ አይደለም፡፡ ለጉባኤ ተሰብስቦ ‹ ለፓትርያርኩ የተጻፈው ደብዳቤ አንጀት አርስ ነው› ብሎ አጨብጭቦ የሚበተን
አመራር ጊዜው ሊያልፍበት ይገባል፡፡ ከዲሚትሪ ሆቴል እስከ ፌዴራል ጉዳዮች የተደረጉትን ውይይቶች ገምግሞ አዲስ አቅጣጫ መያዝ ይገባ
ነበር፡፡ የሚሰበሰብ ብቻ ሳይሆን የሚተነብይ አመራርም ያስፈልጋል፤ ካልሆነ ግን
‹ከክምር ድንጋይ ላይ ይበቅላል ደደኾ
የፈራሁት ነገር መጣ ድኾ ድኾ› የተባለው ይደርሳል፡፡
Thank you for the timely analysis, It is high time for Holly Synod members and Government officials to take corrective measure and build up the broken heart of EOTC followers!
ReplyDeleteዳያቁን ዳኔል እግዚያብሔር የአገልግሎት ዘመንሕን ይባርክ
Deleteዛሬ ዛሬ ክሕነት,ምንኩስና ማለት ግራ እያጋባን ነዉ: ድሮ ድሮ መስቀል ጨብጦ ቆብ ደፍቶ እና ካባ የለበሰ ካሕን ስናይ መንፈስቅዱስን ያገኘን ያሕል ጉልበታቸውንና የጨበጡትን መስቀል ለመሳም የናቱ ጡት ናፍቆ እንዳገኘ ሕፃን እንሰፈሰፍ ነበር: ዛሬ ግን አንዳንድ ካሕናት ከምናየው ድርጊታቸው አንፃር መስቀላቸውን እንደጦር ካባቸው እንደ ሀዘንቤት ድንኲን መፍራት ጀምረናል: እግዚኦ ማረነ ክርስቶስ!!
Dear Dn. Daniel my honest comment for you.....
DeleteIn as many ways as I learn from you and admire your outlook, I am some times offended by your good ideas for improvement of the leadership of MK. I wonder why you do not be part of the leadership as you were previously. What would you be doing if you have been told that the exhibition has been blocked for good reasons. May be I didn't understand your point but it gave me the impression that you want a clear blood shade is the solution. Personally, I am not affraid of such a sacrifice to the well being of the church. But don't you think that it is premature now while we are eventually going there. There will come a time where we the children of God, children of the church will be betrayed by the government and by the unbelievers surrounding us. We shall never do the same to them but keep silent like the sheep. But we won't keep silent from our prayers and blessed deeds.
ዳኒ ትንሽ ጠንከር አላልክም…
ReplyDeleteDani
ReplyDeleteI think this is the perfect time for you to be with MK's leaders more than ever.
የፓትርያርኩ ብእር ግን ምእመናንን የሚያጽናና ጦማር ለመጻፍ ወይም ድንግልን የሚያመሰግን ድርሳን ለመድረስ የሚጨበጥ አይደለም፡፡ እንደ ጠንቋይ ብዕር ለማፍዘዝና ለማደንገዝ እንጂ፡፡
ReplyDeleteችግሩ ሁሉ እየተፈጠረ ያለው በመንግሥት ስም ነው፡፡ ‹መንግሥት አዞናል፤ እገሌ የተባለ ባለ ሥልጣን ብሎናል፤ ፖሊስ እንጠራለን፤ ደኅንነት እናዛለን› ነው በቤተ ክህነቱ ዘንድ የሚባለው፡፡ እውነት መንግሥት በስሙ የሚሠራውን ያውቀዋል፤ ካወቀውስ ዝም ይላል? ቤተ ክህነቱ በሚያመጣው ዳፋ መከራ ለመቀበልስ ዝግጁ ነው? ይህ አካሄድስ ለሀገሪቱ ደኅንነት የሚበጅ ነው? ዐውደ ርእዩ እንዲዘጋ ያዘዘውስ የትኛው መንግሥት ነው? አንዱ የሚፈቅድ ሌላው የሚዘጋ ስንት መንግሥት ነው ያለው? ወይስ ‹ደብዳቤ መጻፉ አላዋጣምና ዝጋልኝ› ተብሎ እጅ የተሰነዘረለት አካል ያደረገው ነው? መጽሐፉ እንደሚል ‹የማይገለጥ የተሠወረ› አይኖርምና ዐውቀነዋልም፣ እናውቀዋለንም፡፡
ReplyDeleteእርሳስና ላጲስ አብረው ይኖራሉ
ReplyDeleteግብራቸው ተቃርኖ የሚጽፈው ከታች
አጥፊው ከላይ ሆኖ '''
Dani I have only words Thank to God!
ReplyDeleteI accept your comments to the Patriarch and the government. But I feel sorry for the comment you gave about leaders of the Mahiber. As you are member, you can tell them face to face rather than writing like this.
ReplyDeleteI believe we all know the true leader of the Mahiber is Holy Spirit! Therefore, it is not very meaningful to worry either the positive or negative attributes of the people serving in the Mahiber. This is a turning point where we have to stop and thing next steps. It is of course high time to have a judicious and patriotic decision wiser than the foolish government people and from those devilish church fathers.
DeleteI believe we all know the true leader of the Mahiber is Holy Spirit! Therefore, it is not very meaningful to worry either the positive or negative attributes of the people serving in the Mahiber. This is a turning point where we have to stop and thing next steps. It is of course high time to have a judicious and patriotic decision wiser than the foolish government people and from those devilish church fathers.
Deleteo may God !
ReplyDelete"ይግባኝ ለክርስቶስ"!
ኦ አምላኬ ስለ ምን ይሁን ዝም ያለን ፣ ማን ከማን ለማስተማር ብለህ ይሆን ፡
ትንሽ ደብዳቤ ልንጽፍ ነበር ግን ማን ያደርስልን ይሆን የአብረሃም፣ የይሳቅ፣ የያዕቆብ አምላክ ሆይ እስኪ ምኑን ተናግረን ምኑን እንተወው እስኪ ጥሩ መሪ እና አስተዋይ ሰው ይስጠን ብለን አንድ ሳምንት ብሱባኤ ላይ ሌላ ሱባኤ የሚቻል ክሆነ እሰኪ ይታወጅ እና እንጩህ ሌላ ምንም የምለው ነገር የለኝም ፡፡
kale hewet yasmalegn
ReplyDeleteአምላከ ገብረ መንፈስ ቅዱስ ይስጥልኝ ዳኒ
ReplyDeleteDeacon Daniel Yeliben Tenagerekewal....Eyasekotun eyegefun new Mengawen Betagne abat eyehonuben new Honewalem Ena Ahun Hulum Gobez Tenekara Tsenuan Hono Betekristiyanun metebek Chigeruwan Lemefetat Yemitebaber Kind Yizo Metebek Alebet Ye mideru Tebaki Eregnawa Titonalena Egna eneberta....Ye mesewatenet Gize new....endalkew Gedel yemineserabet wekte newena Eneberta...Mahiberum Zemenun weketun bedenb yiwaj Tire amerar yiset Egzer yimesegen sew tikitem behon aferetowal yitekemebet. Egziabher ewenetegna abat yiseten Endisetenem sera enesera
ReplyDeleteegizbaher zeme aylem...lehulum mefthewe bersu egee newana....betslote mebrate enwe...dn daniel egizbaher yebrkhe
ReplyDeleteWe all should stand for our church's dignity. Bless u Dany.
ReplyDeleteWe all should stand for our church's dignity. Bless u Dany.
ReplyDeleteዲ/ን ዳንኤል እግዚአብሔር ይስጥልን፡፡ እውነተህን ነው፡፡ ፓትርያርኩ ለኛ ለክርስቲያኖች መቆምን ትተው ለመናፍቃን እና ለፖለቲካ እየወገኑ ናቸው፡፡ እየሰሩ ያሉት ስራዎች በሙሉ ሰውን የሚያነቃቃ ለሃይማኖት እንዲቆም ያደርጋል የሚል ሀሳብ አለኝ፡፡
ReplyDelete".....ለዚህማ ሰይጣን እንጂ አባት አያስፈልግም" .....ተጠቂነት ክርክርና ውይይት፣ ማስረጃና መረጃ አይጠይቅም፡፡ መጠቃቱን ያወቀ ሁሉ ራሱ ገብቶት ይተባበራልና፡፡ ምናልባትም ምእመናንን ከገድል ተራኪነት ወደ ገድል ሠሪነት ያሻግራቸው ይሆናል፡፡ ‹እዚያም ቤት እሳት አለ› አሉ አለቃ፡፡"....Egziabhere Abatim Mengistim Yihunen Ye sewunma ayenew!
ReplyDeleteሐሳብና ርእዮት ሊያስተባብረው የማይችለውን ተጠቂነት ያስተባብረዋል፡፡ ተጠቂነት ክርክርና ውይይት፣ ማስረጃና መረጃ አይጠይቅም፡፡ መጠቃቱን ያወቀ ሁሉ ራሱ ገብቶት ይተባበራልና፡፡ ምናልባትም ምእመናንን ከገድል ተራኪነት ወደ ገድል ሠሪነት ያሻግራቸው ይሆናል፡፡
ReplyDeletegood idea thank you..... we you should work together
ReplyDeleteየቤተ ክርስቲያን አምላክ ይጠብቅህ ዳኒ። እውነት የቅዱሳን አምላክ ዝም ይል ይሆን? እንዴት አባት ለልጆቹ ፈተና ይሆናል? ስለዚህች ቤተክርስቲያን ሌት ተቀን የሚያነቡ የእውነተኞች እረኞች እንባ የምእመናን አዘን መልስ ሩቅ አይሆንም። ይብላኝ አባት ተብዬው አባት
ReplyDeleteዲ/ን ዳንኤል እግዚአብሔር ይስጥልን ፡፡ይህ የማኅበሩ ብቻ ሳይሆን የሁሉም የተዋህዶ ልጆች ጉዳይ መሆን አለበት፡፡የእነ አጼ ሱስንዮስ ዘመን ምዕመን ተመልሶ መጥተው ዳግም ሞተው ተዋህዶን አያጸኑዋትምና ፡፡
ReplyDeleteእውነት ነው፡፡፡፡ እኛ የቤተክርስቲያን ልጆች እንዴት እንደ እርግብ የዋሆች እንደ እባብ ልባሞች በተክክል መሆን ያለንበት ትክክለኛ ጊዜ
ReplyDeleteየሰማዕታቱ አባትና አምላክ ሆይ ስለስምህ ብለው የወደቁ አንተም በስማቸው ትጠራ ዘንድ የወደድህ ስለኛ አይደለም ስለስምህና ስለወደድሃቸው ብለህ ቤትህን ከተኩላ ትጠብቅልን ዘንድ እንለምናለን!!!አሜን!!!
ReplyDelete"የገዛ ፓትርያርካችን ለእኛ ለምእመናን ድኅነትን እንዳናገኝ ሥጋት ሆነውብናል፡፡ የታገሡትን ሁሉ ለክፋት በማነሣሣት ደግሞ ለሀገሪቱ ደኅንነት ሥጋት እየሆኑ ነው፡፡ የምእመናኑን ሥጋት ሲኖዶሱ፤ የሀገሪቱንም ሥጋት መንግሥቱ ሊያስቡበት ይገባል፡፡ ከቤተ መቅደስ የተነሣ ችግር መጀመሪያው እንጂ መጨረሻው አይታወቅምና፡፡ እንዲህ ያሉ ነገሮች የምእመኑን የአስተሳሰብ ቅርጽ ይቀይራሉ፡፡ የሐበሻን ሥነ ልቡና ለሚረዳ ደግሞ ሲረገጥ እንደሚጠክር ጭቃ ያጠነክራሉ፡፡ ሲሞረድ እንደሚሳል ቢላዋ፣ ሲቀረጽ እንደሚሾል እርሳስ ያደርጋሉ፡፡ በዐውደ ርእዩ የሚማሩት የሚያዩት ብቻ ነበሩ፡፡ አሁን ግን ያላዩትም እንዲማሩ አድርገዋል፡፡ ሐሳብና ርእዮት ሊያስተባብረው የማይችለውን ተጠቂነት ያስተባብረዋል፡፡ ተጠቂነት ክርክርና ውይይት፣ ማስረጃና መረጃ አይጠይቅም፡፡ መጠቃቱን ያወቀ ሁሉ ራሱ ገብቶት ይተባበራልና፡፡ ምናልባትም ምእመናንን ከገድል ተራኪነት ወደ ገድል ሠሪነት ያሻግራቸው ይሆናል፡፡ ‹እዚያም ቤት እሳት አለ› አሉ አለቃ፡፡"
ReplyDeleteእግዚአብሔር ይጠብቅህ፤ ሌላ ምንም ቃል የለኝም፡፡ ክፉ አይንካህ፡፡
Aye daniel ye_kend gizea manew le mi_emenan bicha new yalew ....kedimom tenekto lihon aychilim
ReplyDelete....lemafendatim eko haji or bahtawi hunew new yemigebu....
anyaways
...በደኅና ጊዜ ትጉኃን አበው የሰበሰቧቸውን ወጣቶች ካልበተንኩ ብሎ እንዴት አንድ ፓትርያርክ ይነሣል....tiru new endoh mastawes kechalachu...aye diro yejero zemen its already pass .....
በዚህ ዘመን አንድን ግለሰብ ወይም ማህበር አስተዋይ ከሚያስብሉት ነገሮች ዋነኛው.. መቅደሙ ነው፡፡
ReplyDeleteከሆነ በኋላ..አሳማኝ የሆኑ ሰበቦች እንኳን ቢኖሩ… ግቡን ካላሳካ ምንም አይጠቅመውም፡፡
ለዛውም በፈተና የተከበበ ማህበር.. ነገሮችን ክፍት መተው..ለእንደዚ አይነት ትልቅ መሰናክል ይዳርጋል፡፡
A meaningless comment!
Deleteእንደ ሶምሶን ከአንበሳ ሬሳ ማር ለማውጣት ግን በሳል አመራር ይጠይቃል፡፡ እግዚአብሔር ይስጥልን፣ ቃለ ሕይወት ያሰማልን፣ ለሁሉም ማስተዋልን ይስጥልን፣ ወንድሜ ጥያቄ ግን አለኝ፣ መፍትሄውን ብንወያይበትና ሀሳቦች ቢቀርቡ?? ድንገት ለማህበሩ የሚበጀው ይመስለኛል፣ ምክንያቱም አሁን አውደርእይ ማታየቱ ላይ ብቻ ሳይሆን ሌላም ተጨማሪ ችግሮች ይታየኛል ይኸውም ምእመኑ እንዲያምጽና በዚህ ስበብ ማህበሩን ለመዝጋት የታሰበ ይመስለኛል፣ እኔ በግሌ የሚታየኝን ነውና፣ ሁሉንም ነገር በጥንቃቄ ብንመለከተውና ብናደርገው ጥሩ ነው ብዬ አስባለሁኝ፣ ጸልዩ በእንተ ልቦና አቡነ ማቲያስ፣
ReplyDeleteእግዚአብሄር ይባርክህ!!
ReplyDeleteወፌ ሆይ ታውቂያለሽ…….
ReplyDeleteጎርፍ ይጎርፍ ነበረ ገና በጠዋቱ
ነፋስም ነበረ ጥንት ከፍጥረቱ
እባብ አለ ዛሬ ልክ እንደ ትላንቱ
እረኛውም ነበር ገና በጥዋቱ
ርግቦችም ነበሩ አንችን ያስገኙቱ
ወፌ ሆይ ልበልሽ ደግሞም ልሞግትሽ
ምስጢር ቢገልጽልሽ…….አንችም መልሽልኝ ከግዕዛንሽ ጠልቀሽ
አንችን ከአስገኙቱ ምን ይሆን የተማርሽ?
አድምጭው ልቅሶ ትንታግሽን…..መሆን ያለመሆኑን የእናት የአባትሽን?
አዎን ያኔ……..
አዎን ያኔ….. ታውቂዋለሽ
እረኛው ጠባቂ በጎች ተጠባቂ የሚሆኑበትን
ለዘር ዘር የሚተርፍ ፍሬ የሚያፈራ ጎጆ አቀላለሱን!
ዲያቆን ዳንኤል ቃለ ሕይወት ያሰማህ፡ አሁንስ የእግዚአብሔር ትዕግስት በዛ ፡ በዚህ የጾም ወቅት ትልቅ ሥራ የሚሰራበት መሆን ሲገባው በእንደዚህ አይነት ተራ ነገር ውስጣችንን ሲጎዱት በጣም ያሳዝናል፡፡ ይብስ አይምጣ አለ አባባ ጎልመሜ ይባላል፡፡እግዚአብሔር ኦርቶዶክስን ይጠብቃት፡፡
ReplyDelete‹‹ስውሩ አመራር›› ብለህ የጻፍከው መጣጥፍ ያመጣብህን ፀፀትና በማኅበሩ አክራሪ ኃይሎች መገፋት ለማስታመም ስትል ግርግር እየጠበቅህ የማኅበሩን አባላት ስሜታዊ የሚያደርግ ጽሑፍ በመጻፍ ትደክማለህ፡፡ስሜት ከመኮርኮር እና ጥቅስ ከማብዛት ከሁለቱም ወገን እየታየ ያለውን የእልህ መንገድ ነቅሰህ መፍትሄ ብታመላክት ይሻላል፡፡ያፈራችሁትና በአርአያችሁ የፈጠራችሁት ትውልድ በያዘው ዘወትር እየተሳደቡ እና በየሚዲያው እየተካሰሱ መኖርን ሙያው አድርጎ እንዲይዝ የሚገፋፋ ጽሑፍ የተወሰኑ ደጋፊዎችን ለማስጨብጨብ እና በስሜታዊነት በታወረ ቁልቁለት ጉዟቸው እንዲቀጥሉ ከማበረታታት የተሻለ ጠቀሜታ የለውም፡፡ጽሑፍህ ከርእሱ እስከ ይዘቱ ክርስቲያናዊ ባልሆነ አነጋገር የተሞላ ነው፡፡የመረጃ ምንጮችህም አሉባልታን እንደቋሚ ሥራ ይዘው ውዥንብር በመዝራት የበለጠ ክርስትና አለን የሚሉ ብሎጎችና ጋዜጦች ናቸው፡፡ለነገሩ በአመራሩ አካባቢ ያሉ ጥቂት ነባር የማኅበረ ቅዱሳንን አባላት የዓመታት ባሕሪ ለታዘበ ሰው ጽሑፍህ አይገርምም፡፡ማኅበረ ቅዱሳን ማለት ቤተክርስቲያን ነው፤ቤተክርስቲያን ማለት ማኅበረቅዱሳን ናት የሚመስል ቤተክርስቲያኗን በማኅበር ተክቶና ንዑስ ክፍል አድርጎ የማየት ግብዝ አመለካከት ስር ከሰደደ ቆይቷል፡፡ከዚህ የውርስ አመለካከት አንተም አልተላቀቅህም፡፡ችግሩ አንድ ወገን ብቻ ዘወትር ነጥሎ በመውቀስና በማሳደድ የሚቀረፍ ፈተና የለም፡፡እንዲሁ ደጋፊና አጨብጫቢ ለማስደሰት ግን ፓትርያርኩ ላይ ያወረድካቸው ቃላት ከበቂ በላይ ናቸው፡፡ደረቅ ስድቦችና ‹‹የጥንቆላ አፍዝ አደንግዝ›› የመሳሰሉ አስነዋሪ ቃላት እንደተጠበቁ ሆነው የአማርኛ ችሎታህን ምን ያህል እንሳደግኸው አሳይተሀል፡፡
ReplyDeleteIf you said Dn Dniel is wrong, why you reply with similar tone and sentence. I never blame and want to blame individual persons, please shut up your mouth we never said Mk is Our Church and Our Church is MK. As human beings and our maturity I can accept any problem that we done. But this time what happened is not like that. It is our Church and faith.Since the case raised to the level of Faith as Abba Agaton said you are the person that said Money is the Church/Faith and the Church/Faith is money.
DeleteI better advise you please evaluate the status of our church, if you are orthodox.
Read the bible, there are times that you should have to say this is white and this is black.
You might think of that Dn Daniel is trying to re work his relationship with Mk. If he is doing so this is the right time, and he is successful.
Do not forget nobody in Mk is against the principle of Mk. That is why everybody is in the church till now. Conflicts happen do you to some circumstances are very healthy in an institution, if it is not on the principle.
Thank you brother. I wish I can meet you
Deleteበመሰረቱ አንተ ለቤተክርስቲያኗ ከሚቆሙት ወገን ስላልሆንክ ስለማህበሩ መናገር አይገባህም። ጽሁፍህ ሦስት ገሮችን ይጠቁማል። አንዱ በማህበሩ ላይ ያለህን ጥላቻ ሁለተኛው ዳንኤል ከማህበሩ ገሰር አለመጣላቱ ሦስተኛው ዳንኤል ከህዝብ ያገኘው ከበሬታና ፍቅር ያስቆጨህ መሆኑን። ከዚያ በተረፈ እንቶፈንቶ ነው። የሚወዱልህ የሉም ማለቴ ግን አይደለም። የተሀድሶና በምሁራን የተዘጋጀውን የቤተክርስቲያንን ሙሰኞች የሚቆጣጠረውን ሕግ በተቀነባበረ ሴራቸው እንዳይሰራ ያደረጉት ሀይሎች አሉልህ።
Deleteበዐውደ ርእዩ የሚማሩት የሚያዩት ብቻ ነበሩ፡፡ አሁን ግን ያላዩትም እንዲማሩ
ReplyDeleteአድርገዋል፡፡ nice view!!!!
I think it is time to show the gov our angry. our executives needs to guide us what need to do in short time. Ebakachihu Atgezgzun, kemotinm tolo memot new. Unless MK is getting weaker and weaker, one day they will come and lock the door.
ReplyDeleteNote for gov official
I think you have to seat down and double check. You never win this game. There is fire every where, the oromia issues, G7 from north and west Ethiopia, Gonder issues, on top of this you are firing the pile of wood now- mahbre Kidusan.
Dear brothers and sisters. No one can lock the MK doors except God. The Mahibere Kidusan is hosted in our heart nobody ever has the power to drive out MK from within our hearts and minds. I really say this as an average Christian. But I believe others-spiritually braver ones can complement me and say a lot more about that truth which drives MK.
DeleteVery shocking, disturbing and irritating news. Personally, I support Mahibere Kidusan in its very objective of saving our church from destruction and Tehadiso. But what is the objective of the Pope? In fact he should have been the one doing such job, if not, he should just be silent or support and encourage the works of MK. Otherwise, standing in the opposite direction reveals that, he like many others, is not guarding the church and its flocks and has a hidden agenda of destroying the Ethiopian Church, the Very Symbol of our Country.
ReplyDeletePlease tell me if there exists any procedure in the Synode to relieve him from being POPE and replace him with true Tewahdo Fathers. He is such a deceitful and hypocrite individual. Let alone being Pope, I doubt his status as a an ordinary follower of the EOTC like us.
By the way Dani, I was very happy to read your post about the Pope.
ReplyDeleteHistory is folding to EXPOSE the very true nature of tigres & their true history and behavior....now, I am talking about the 99.9999% of the tigres....tigres know how to become a junta, a thief, a cadre, a corrupt, a controbandist, an ethnocentric, brainwashed, hidden killer....believe me not how to become a believer, a lover, peace maker, an brave Ethiopian...Look, all these are behaviours of satan and its followers, not the behaviours of a believer....That is why even the PATRIARCH is serving as a cadre....he got the chance to be a PATRIARCH but still serves for satan as a cadre....God gives everything and calls everyone to serve Him, but people reject the call for their curse!!!.....even the previous dead paulos was same....he contributed money for election!....WHAT A CURSE!!!....ever since their arrival from Yemen as daily laborers, tigres don't have a country to base their origin but what is known is that they have a destination....only a very very very small number of tigres are Ethiopians and these are suffering just because they are Ethiopians...just because they are believers!....the Church and mosques are being divided by the cadre tigres....astewulu....here, I declare that cadre Mathias is not a church father....he is a cadre of weyanes....look, Ariyos and Nistoros were church fathers, but now no longer!!!...same thing has to be be DONE to cadre Mathias....just allow me to shoot him....THIS TIME IS GOOD FOR TRUE CHRISTIANS b/c getting the chance of killed fighting for Christianity, as a MARTYR, is almost at the door and hand of Christians!....hey, WAKE UP...I would rather die as a martyr than to see the fall of church. Betekrstain kemtefers gelaye yifres!!!...CHRISTIANITY doesn't base itself on ethnicity....you won't be asked your race when you stand in from if Christ Jesus....so, I ask every Ethiopian Christian to cone together and act together to DESTROY weyane and its cadres together!!!!....kale hiwot yasemalene wendemachin Deacon Daniel....behiwot yaleh sema'et NEH...Egziabher yitebeqehe!
ReplyDeleteየእስራኤል የእነ ዳዊት አምላክ አብዝቶ አብዝቶ ይባርክህ አንጀቴን አራስከዉ በእዉነት ዳንኤል ተባረክ ብሩክ ሁን .. አፎይ ተነፈስክሁ///////
ReplyDeleteKale Hiwot Yasemalen Endih yale yekurt ken lij lebetekrestian Yasfelegatal!!!
ReplyDeleteአሉባልታ ሰምተው እውነት ነው እያሉ፣
ReplyDeleteያሰባቂን ወሬ እየተቀበሉ፣
መግባባት ቀረና ከረረ ነገሩ፣
አባትና ልጅ ተቆራርጠው ቀሩ የሚለዉ ተረት ሰሞኑን ቦታዉን ያገኘ ይመስለኛል በማህበረ ቅዱሳን እና በአቡነ ማትያስ በኩል
እግዚአብሔር የቤተክርስቲያናችንን አንድነት ይጠብቅ! አሜን!!! ዳንኤል፣ አንተንም እግዚብሔር ይባርክህ!
ReplyDeleteእግዚአብሔር የቤተክርስቲያናችንን አንድነት ይጠብቅ! አሜን!!! ዳንኤል፣ አንተንም እግዚብሔር ይባርክህ!
ReplyDeleteፓትርያርክ ማለት በግሪክ ‹ታላቅ አባት› ማለት ነው፡፡ የታላቅ አባት ተግባር የልጆቹን ሥራ ማፍረስ አይደለም፤ ለዚህማ አባት አያስፈልግም ሰይጣን እንጂ፤
ReplyDeleteእምቢ ማለት መልካም የሚሆንበት ግዜ አለ በተለይ የጽድቅን ስራ፣ የእግዚአብሔርን ወንጌል ለማስፋፋት የሚከለክል ችግር ሲገጥም፣ፍትህ ሲጓደል ወዘተ።ሁልግዜ ለእግዚአብሔር እና ለቤተክርስቲያን ስርአት መወገን ተገቢ ነው፤ከስርአት ያፈነገጠ ነገር ሲገጥመን ለዶግማው ለቀኖናው መቆም ያሻል፤መጥምቀ መለኮት ዮሃንስን አንገቱ እንዲቀላ ያደረገው ሄሮድስ የወንድሙን ሚስት ማግባቱ ከስርአት ያፈነገጠ እግዚአብሔርን ደስ የማያሰኝ መሆኑን በመናገር መገሰጹ ነው።አሁንም ዘርን ሳይሆን ስርአትን ያማከለ ምእመኑን ከእውነት ማለት ከእግዚአብሔር ጋር አንዲጣበቅ የጳውሎስ ነኝ የአጵሎስ ነኝ ሳይሉ በአንድነት ከስርአት ያፈነገጡ አካሄዶችን ቅዱስ ሲኖዶሱ ሃላፊነት ወስዶ እንዲያስተካክል ግፊት ማድረግ ተገቢ ነው፤ግፊቱ በምን መልኩ ቢሆን ይሻላል የሚለውን ማጥናት ተገቢ ነው።ይህ ሲሆን ያለአግባብ በአዲስ አበባ አድባራት የተከማቹ ካህናት ቀንደኛ ተቃዋሚ ሊሆኑ ይችላሉ ምክኒያቱም እንዲመጣ የሚፈለገው አስተዳደራዊ ሪፎርም የእነኚህን ካህናት ጥቅም ይነካል፤እንዴት ቢሉ ሪፎርሙ የካህናት የደሞዝ አከፋፈል ወጥነት እንዲኖረው ይጠይቃልና፤የደሞዝ አከፋፈሉ ወጥነት እንዲኖረው ከተፈለገ ከአዲሳበባ አድባራት የህንጻ ኪራዮች እና ሌሎች ገቢወች የሚገኘውን ገንዘብ ፍትሃዊ በሆነ መንገድ መጠቀምን ይጠይቃል ይህ ደግሞ ከካህናት ቅነሳ እስከ በኣዲሳበባ ዙሪያ ባሉ ካህናት የሌላቸው ቤተክርስቲያናት እነኝህን ካህናት ማሰማራት ይጠይቃል ከእነኝህም ካህናት ተቃውሞ ይገጥማል፤የቤተክርስቲያንን ህንጻወች እና ቦታወች በብላሽ ተከራይተው የሚገለገሉ ባለሃብቶች አሁንም ቀንደኛ ተቃዋሚወች ይሆናሉ እነዚህ ባለሃብቶች በቤተክርስቲያኗ አስተዳደራዊ ስራ ውስጥ ያላቸው አሉታዊ ሚና ቀላል አይደለም፤ሌላው ቀደም ብየ እንደገለጽኩት በማወቅም ባለማወቅም ጉዳዩን የዘር ለማድረግ የሚሞክሩ እና የኣጥቂ ዕና የተጠቂ ዘር እንዳለ የሚያናፍሱ አካላት ለፍትህ እንቅፋት ይሆናሉ ስለዚህ በቅድሚያ እዚህ ላይ አጥብቆ መስራት ያስፈልጋል፤ዋናው አላማ ቤተክርስቲያንን በአወንታዊ የሁሉም ነገር አብነት ማድረግ ነውና።ይህ ከመሆኑ በፊት የሚደረግ ማንኛውም እንቅስቃሴ ውጤታማ አይሆንም ወይም በሌላ አላማ ይጠለፋል።ከዚህ ሁሉ በፊት ግን ጾሙን በትጋት በመጸለይ እና በመጾም ማሳለፍ ተገቢ ነው።
ReplyDeleteቃለ ህይወት ያሰማልን ድያቆን ዳንኤል፡ እንግዲህ ምን እንላለን እግዚኣብሄር ቤተክርስትያኑን ይጠብቅ፡እንደ ኣቡነ ኣትናቴዎስ ዘእስክንድርያ፡እንደ ኣቡነ ጎርጎርዮስ ዘኢትዮጵያ የመሳሰሉ ኣበው ያስነሳልን ነው የሚባለው
ReplyDeleteማኅበሩማ በመተንበይ ከአንድ ዓመት በፊት ቀድሞ ተዘጋጅቶ አልነበረም እንዴ!
ReplyDeleteሌሎች እንደሚሉት ምንም ስራ መስራት አልነበረበትም ካልተባለ¡
Yene Jegna, Egziabher Amlak birtatun ystih. Lidersbih yemichlew chigir sayhon yemiemenan chigir asasboh, bedfret sletenagerk ena slastemark ye ewunet Amlak ytebikih, lia min elalehu.
ReplyDeleteZinabie Feleke negn.
Kalehiwot yasemalin kelbe erekchialehu lemetebekbign neger hulu yebekulen zgiju negn eskemeche daradar eyalne enoralenyabetewu yfret!!!!
ReplyDeleteDany memochahen Nekahew !!
ReplyDeleteየሚሰበሰብ ብቻ ሳይሆን የሚተነብይ አመራርም ያስፈልጋል፤ ካልሆነ ግን
ReplyDelete‹ከክምር ድንጋይ ላይ ይበቅላል ደደኾ
የፈራሁት ነገር መጣ ድኾ ድኾ› የተባለው ይደርሳል፡
‹ኦርቶዶክሳውያን ጳጳሳት አምስት ተልዕኮ አላቸው፡፡ እነዚህም
ReplyDelete1. ወንጌልን መስበክ(Preach the Gospel)
2. ምሥጢራተ ቤተ ክርስቲያንን መፈጸም(Administer the Sacraments of the Gospel.)
3. የቤተ ክርስቲያንን እምነት፣ አንድነትና ቀኖና መጠበቅ(Guard the faith, unity, and discipline of the church.)
4. ለካህናትና ለምእመናን የቅድስና ምሳሌ መሆን(Be a moral example of holiness and wholesomeness.)
5. በእረኛውና በበጎች መካከል ያለውን ክፍተት ማጠበብ(Diminish the distance between bishops and their flock.)
‹ከክምር ድንጋይ ላይ ይበቅላል ደደኾ
ReplyDeleteየፈራሁት ነገር መጣ ድኾ ድኾ›
Pop Francis Washes Feet of Refugees for Eastern.
ReplyDeleteAbune Mathias ዓላማው ግን ማበሳጨት፣ ዐመጽ ማስነሣት፣ ተሥፋ ማስቆረጥና ምእመናንን ወደማይፈልጉት መሥመር መውሰድ ነው፡፡ ለዚህ ነው ፈያታዊ ዘየማን ገነት በገባባት ሰዓት ዐውደ ርእዩ እንዲዘጋ የተደረገው፡፡
አንተ አሳርፋቸዉ
ReplyDeleteድርሻችንን ልናዉቅ ቤተ ክርስቲያን ስትጠራን፣
መንገዱን ከዘጉ ተማክረዉ ከሰይጣን፣
ከጠላት ጋር ማበር ከሆነ ድርሻቸዉ፣
የአብርሃም አምላክ ዋጋቸዉን ስጣቸዉ።
መንጋ ጠባቂነት ቀንበሩ ከብዷቸዉ፣
የገንዘብ የስልጣን ህመም ካገኛቸዉ፣
ከተንገዳገዱ መቆም ካቃታቸዉ፣
እኛ አቅም የለንም አንተ አሳርፋቸዉ።
ገንዘብ ካመለኩ ለሆዳቸዉ ካደሩ፣
ከጠላት ተባብረዉ ለጥፋት ካሤሩ፣
የበሉበትን ወጭት ከሰበሩ፣
አምላክ ሆይ ማራቸው ይፈቱ ከእሥሩ።
በቀን ለሚቃዡ ታሪክ ተረስቷቸዉ፣
እሷ ስትጠፋ የምያዩ መስሏቸዉ፣
በከንቱ ሲደክሙ እንዳይመሽባቸዉ፣
የቤተ ክርስቲያን አምላክ አንተ ይቅር በላቸዉ።
ለወንጌል መስፋፋት መንገዱን ከዘጉ፣
ቀንና ሌሊቱን ለጥፋት ከተጉ፣
ልባቸዉ በገንዘብ ስልጣን ከተፈታ፣
አምላክ ሆይ ማራቸዉ ገመዳቸዉን ፍታ።
ተመሳስሎ ገብቶ መንጋዉን ለማወክ፣
መኖርህን ዘንግቶ የጴጥሮስ አምላክ፣
አስቸግሯልና እባክህ ለይልን፣
አንተ ታዉቃለህ በግና ፍየሉን።
ነጣቂ ተኩላ የበግ ለምድ ለባሾች፣
ሆነዉ ከተገኙ አጥፍተዉ ጠፊዎች፣
አንተን ካሳደዱ አዕምሮ ካጡ፣
እባክህ ጥራቸዉ ወዳንተ እንዲመጡ።
(ኃይለገብርኤል፤ ከእንግሊዝ)
It is a good start to stand firm and together. We will be even better.
ReplyDeleteIt is a good start to stand firm and together. We will be even better.
ReplyDeleteAbsolutely! Amlak Yirdan. Antem tebarek. Ewnetim Daniel.
ReplyDeleteThis is true, I agree with your points. God Bless you!!
ReplyDeleteIt was very painful for me too know about this writing through shared facebook posts. I really am sad to see my fathers being insulted in a way that is unimaginable. First by Tadesse Weku the Patriarch being lower than the husband of a steeper. And now by Dn. Daniel Kibret, the patriarch's writings and words compared to the writings of a Witchcraft"የፓትርያርኩ ብእር ግን ምእመናንን የሚያጽናና ጦማር ለመጻፍ ወይም ድንግልን የሚያመሰግን ድርሳን ለመድረስ የሚጨበጥ አይደለም፡፡ እንደ ጠንቋይ ብዕር ለማፍዘዝና ለማደንገዝ እንጂ፡፡"....and the Holy Patriarch itself mentioned as a dead lion "እንደ ሶምሶን ከአንበሳ ሬሳ ማር ለማውጣት ግን በሳል አመራር ይጠይቃል፡፡".
ReplyDeleteወንድም ዳንኤል። እኔ እኔ የተዐድሶ አቀንቃኝ ነኝ። ቤተ ክርስቲያኖ ወደ ቀደመው ዉበቷ መመለስ አለባት። ከተረት ተረት መውጣት አለብን። ቀርቦ መነጋገሩ ደግሞ አንዱ መፍትኤ ነው። ጌታ እየሱስ ይጎብኘን። አክባሪኽ ነኝ።
ReplyDeleteአንተ ልጅ እግዚአብሔር አገልግሎትህን ይባርክ። ጽሑፍህን በእንባ አነበብኩት ፤ ቤተ ክርስትያንን ከማዕዷ የሚበሉ፣ በክብር መናብርቶቿ ላይ የሚቀመጡ፣ባልተገባቸው የከብር ወይም የቅድስና ስም የሚጠሩ እኩያን የሚመሩበት( መሩ ካልን) ወይም የሚያፈርሱበት ዘመን ላይ ነው ያለነው። እነሱ ያመኑበትን ማድረጋቸው አይገርምም። የሚገርመው ያመንበትን ክርስቶስ የሞተለትን እኛም የቆምንበት ወይም የቆምንለትን ዓላማ ሲንዱ እና ሲያፈርሱ በዝምታ ማየታችን ነው። " Cowards die many times before their death. " እንዳለው ሸክስፒር ልንሞትለት የሚገባን ዓላማ ሲሞት እያዬነው ስንቶቻችን ደጋግመን በፍርሃት ሞትን? ክርስቶስ የሞተለት ዓላማ ፣ ሰማዕታት ደማቸውን ያፈሰሱላት ቤተ ክርስቲያን ፣ ጻድቃን በብዙ ድካም ያቆዩት
ReplyDeleteክርስቲያናዊ አስተምህሮ እና ትውፊት ሲቀሰጥ ፣ገንዘብና ንብረቷ ሲዘረፍ፣ ልጆቿ ከውስጥ ገፊ ከውጭ ዘራፊ እየተቀባበለ ሲናጠቃቸው ፣ ራሱን ገልፆ ዓላማ ቀርጾ ከውጭ ከሚወጋት የለየለት ጠላት በከፋ በጥቅሟ የሚኖሩ ፣ በእቅፏ ያሉ አባት ወይም አራዊት መሆናቸው ባለየለት የውስጥ ጠላቶች ይበልጥ ስትደማ ከማየት በላይ መሞት ምንድነው? ስንት ጊዜ እንሙት? ለምን ያህል ጊዜስ እንሙት ? በዝምታ ሞትን ፣ በይሉኝታ ሞትን፣ በዘር፣ በጎጥ ፣ በመንደር፣ በቡድን እና በዘውግ ሥሌት ከእውነት ተጣልተን ሞትን። ለመሆኑ የሞታችን ፋይዳ ምንድነው?ሰማዕታት ቢሞቱ ቤተ ክርስቲያንን በደማቸው አድምቀው ስማቸውን በሕይወት መጽሐፍ አጽፈው ነው፤ ክርስቶስ ቢሞት በነጻነት እንድንኖር ነፃነትን ሊሰጠን ነው። ያ ነጻነት ደግሞ ሞት የሞተበት ነፃነት ነው። ታዲያ ለምን በሞተ የሞት ቀንበር ስር ወድቀን ዳግም እንሙት? " አንተ የምትተኛ ንቃ ከሙታንም ተነስ ክርስቶስ ያበራልሃል" ኤፌ 5፥14
እንዳለው ብርሃነ ዓለም ቅዱስ ጳውሎስ። በዓላማ የሚያጠፋን ሰው በይሉኝታ ወይም በዝምታ ማስቆም አይቻልም ።አቋም ይዞ መታገል ያስፈልጋል ። ዝምታ ወይም ይሉኝታ በራሱ ተባባሪነት ነው ።
ሐሰትን መተባበር ደግሞ ሞት ነው ፣ መራራ ሞት።
እንቢ ማለት ፣ በቃን ማለት፣ በቃችሁም ማለት ያስፈልጋል። መንግስት በብዙ በሳል አዕምሮዎች የሚሰራ አስተዋይ መዋቅር ነው። ይህንን እሳት ከዚህ በላይ እንዲነድ ከዚህም በላይ እንዲያቃጥለን የሚፈቅድ አይመስለኝም። ከፈቀደ ግን ያልተበደረውን ሒሳብ ሊያወራርድ ይችላል። የቤተክርስቲያኒቱን መዋቅር ፣ማኀተምና የፕሮቶኮል መዝገብ ስለተቆጣጠሩት ብቻ ገርፈው ግርፋቱን በትዕግስት ችሎ ዝም ካለው ተበዳይ ቀድመው በአድራሻም ሆነ በግልባጭ የጩኸት ድምጽ ስላሰሙት እውነትን ሳይመረምር የአጥፈ ደጋፊ ከሆነ ምርጫው የራሱ ነው እኛ ግን በቃን ማለት አለብን። ከዚህ በላይ ምን ይሁን ? ምንስ ነው የምንጠብቀው? ትዕግስት አጥፊ ወይም በዳዩን ቀይሮ ወደ ህሊናው ማምጣት ካልቻለ
ስሙ ፍርሃት ነው። ፍርሃት ደግሞ ሞት ነው። ትርፍ የለሽ ሞት እየሞቱ ለመኖር ምን ትዕግስት አለው?
Love you Dani ! you are the rock !
ReplyDeleteI have been reading your blog since the beginning ,but this one is way above the roof in terms of talking to our own mess house. Thank you Dani as always.
ReplyDeleteየኛ እረኛ ሠው ሣይሆን የማያንቀላፍው የድንግል ልጅ ክርስቶስ እየሱስ ነው!!! አባ ማትያስ አነጣጥፍው ይተኙ!!! ድሮስ በእጅ ብልጫ እንጅ በጌታ ፈቃድ አልተመረጡ!!
ReplyDeleteyehun , Esty BeTsomu Seytan Endyh yeFetinen . .
ReplyDeleteyehun Esty, BeTsomu Endyh Seytan yeFetinen . .
ReplyDeleteSelam Dn Daniel,
ReplyDeleteThanks for the info, aren't you too late to make these important comments on the the over all conditions of the Church?
Thank you Dani
ReplyDeleteቃለ ህይወት ያሰማልን።
ReplyDeleteፈያታዊ ዘየማን ገነት በገባባት ሰዓት ዐውደ ርእዩ እንዲዘጋ ተደረገ፡፡
ReplyDeleteEGZIABHER hoy melkamun awken endiniguaz erdan. Libonachininim abralin. Memihirachini kalehiwot yasemalin.
ReplyDeleteከጸሎት ጋር ብልህ መሪ የሚያስፈልግበት ሰኣት አሁን ነው፡፡ ለአባታችንም ልብ ይስጥልን፡፡
ReplyDeleteMinew abate balek gize ,engdhe bezachn kerbawl
ReplyDeleteበአንድ ወቅት ከባለ ቅኔው መጋቤ ምስጢር ወልደ ሩፋኤል ፈታሒ ጋር ሻይ ቡና እያልን ስናወጋ ዲ/ን ዳንኤል ይህን አጋጣሚ መጠቀም የፈለገ ይመስላል። ደጋግሞ ይጠይቀዋል። በዚህ መካከል አንድ ስጋቱን እንዲህ አጫወተን። አንዷን ጥያቄ ልምዘዝ "ከአቡነ ጳውሎስ በኋላ ማን ይሾም ይመስልሀል?" ፊቱ ጭፍግግ አለ። መልስ በጉንጩ የሆነ መጋቤ ምስጢርን ያህል ሰው የትካዜ ጊዜ ወሰደ። እናም መልሶ ጠየቀ "አይ እስከዚያ እንኖር ይሆን?" ግምቱ የብዙዎቻችን ዓይነት ነበር። ደሞ ቅመም የሆነ ጨዋታውን አከለበት። "ሽማግሌውን ሁሉ ሸኙት እኮ ማን ቀራቸው? ስጋቴ ግን።" አለና ትንቢት ልበለውና ለጊዜው እንደዋዛ ስጋቴ ነው ያለውን አሳብ ተነፈሰው። መጋቤ ምስጢር ሰው ፈልጎ ያጣ ያህል አንገቱን እየወዘወዘ "ስጋቴ ግን በኋላ የሚሾመው አቡነ ጳውሎስን የሚያስመሰግን እንዳይሆን ነው።" አለን። ዳኒ ታስታውሳለህ? ይህን ካለ በኋላ አንተም የዝምታ ጊዜ ወስደህ ነበር ሌላ ጥያቄ ያነሳኽው። የባለ ቅኔው ትንቢት ተፈጸመ።
ReplyDelete‹ባለሞያ ሴት የሠፋችውን ወራንታ፣ ጅል ትተረትረዋለች›
ReplyDeleteበሱራፊ ነበልባል የተዘጋች ገነት ስትከፈት በፓትርያርክ የተዘጋች የቤተ ክህነት በር ልትከፈት አልቻለችም፡፡ ሰይጣንን ከእግዚአብሔር ጋር ለማነጋገር የደከሙ እነ ክርስቶስ ሠምራን የመሰሉ ቅዱሳን ባሉባት ቤተ ክርስቲያን እረኛው ከመንጋው ጋር መነጋገር አቃተው፡፡ ኢየሱሳውያንን በዐደባባይ ሳናነጋግራቸው መሄድ የለባቸውም ብለው የተሟገቱ እነ እጨጌ በትረ ጊዮርጊስ በነበሩባት ቤተ ክርስቲያን የገዛ ልጆቹን ለማነጋገር በር የሚዘጋ እጨጌ ተፈጠረ፡፡ የመካ ቁራይሾችን አሳልፈን ለጠላቶቻቸው አንሰጥም የሚሉ አበው በነበሩባት ቤተ ክርስቲያን የገዛ ልጆቹን አሳልፎ የሚሰጥ አባት መጣ፡፡
ReplyDeleteመናፍቃንን የሚተች ጽሑፍ በኦርቶዶሳውያን ተጻፈ ሲሏቸው፤ ምእመናንን የሚያጸና ጉባኤ ሊዘጋጅ ነው ሲሏቸው፤ ሕዝቡ ወደ ቤተ ክርስቲያን እየመጣ ነው ሲሏቸው፤ ወጣቱ ትውልድ ቤተ ክርስቲያኑን ለማገልገል እየተጋ ነው ሲሏቸው፤ ዲያስጶራው ሕዝብ በእናት ቤተ ክርስቲያን ሥር ሆነ ሲሏቸው፤ ቤተ ክርስቲያንን የሚገልጥ ዐውደ ርእይ ሊዘጋጅ ነው ሲሏቸው፤ መንፈሳዊ የቴሌቭዥን ፕሮግራም ሊቀርብ ነው ሲሏቸው ያን ጊዜ ብዕራቸውን ይዘው ለማገድና ለመክሰስ ይነቃሉ፡፡
ReplyDeletewoy gud
ReplyDeleteዬ፣ ዬ፣ ዬ
ReplyDeleteበዐውደ ርእዩ የሚማሩት የሚያዩት ብቻ ነበሩ፡፡ አሁን ግን ያላዩትም እንዲማሩ አድርገዋል፡፡
ReplyDeleteምእመናንን ከገድል ተራኪነት ወደ ገድል ሠሪነት ያሻግራቸው ይሆናል፡፡ ‹እዚያም ቤት እሳት አለ› አሉ አለቃ፡፡
ReplyDeleteየፓትርያርክ ማትያስ ዘመን እንደ ፓትርያርክ ጳውሎስ፣ የጠቅላይ ሚኒስትር ኃይለ ማርያምም ዘመን እንደ ጠቅላይ ሚኒስትር መለስ አይደለም
ReplyDeleteእንዲህ እውነት እውነት እያወራን፥ የተሻለውን ማድረግ ይገባናል። ለረጅም ዘመን እየገደለን ያለው በመካከላችን የምንፈጥረው ክፍተት ነው፤ አገልጋይ አገልግሎቱን ሲያስታጉል የማይጠየቅበት፣ ተገልጋይም ግልጋሎቱ ሲጓደልበት የማይጠይቅበት አካሄድ። ይህን ክፍተት ለመድፈንና ለማጥበብ ደግሞ እንዲህ እውነት እውነቱን መነጋገር ይገባናል። የሚጠየቀው ተጠይቆ፣ የሚያጠፋው ተገስጾ፥ መስተካከል ያለባቸው ነገሮች መስተካከል ይኖርባቸዋል፥ የላቀው ጥፋት ከመምጣቱ በፊት። እግዚአብሔር አምላክ ለሁላችን መንገዱስ ያሳየንና በመልካሙ እንድንተባበር ያድርገን።
ReplyDeleteእግዚአብሔር ይስጥልን ወንድማችን።
በመጀመሪያ ደረጃ ሙአዘ ጥበብ ዳንኤል ክብረትን የመሰለ የሃገራችንም ሆነ የቤተክርስቲያናችን ታላቅ ሰው የፃፈውን ፅሁፍ ላይ እንደ ቀላል ነገር ኮሜንት መስጠቱ በጣም ከባድ ቢሆንም ነገር ግን ጉዳዩ በጣም ከባድና ማንም ኦርቶዶክስ ክርስቲያን ነኝ ብሎ ሚያስብን በሙሉ የሚመለከት ጉዳይ ስለሆነ ይህቺን ኮሜንት ለመፀፍ ተገድጃለሁ፡፡ በአሁኑ ሰዓት ሁሉም የጥፋት ሰራዊት ቤተክርስቲያናችንን ለመቦጥቦጥ አሰፍስፎ በሚጠባበቅበት ጊዜ የተፈጠረው ነገር በጣም አሳዛኝና በታሪክም አሳፋሪ ሁኖ ተመልክቼዋለሁ፡፡ በማንኛውም ሰው ሐይማኖታዊ መረዳት መሰረት የአውደ ርዕዩ ክፋት ምንድን ነው? የሚያስከትለው አሉታዊ ተፀዕኖ ምንድን ነው? እንዲህ አይነቱን በጎ አስተዋፅኦ ያለውን አውደርዕይ ለማገድም ሆነ ለማሳገድ ማሰብ በራሱ ቤተክርስቲያኗን ለተኩላዎች አሳልፎ ከመስጠት የማይተናነስ አሳፋሪና ሰይጣናዊ ተግባር መሆኑን እገነዘበዋላሁ፡፡ የድሮዎቹ አባቶቻችን ክፉ አመሎቻችንን በውስጥ ደብቀው ይዘው ገመናችን ሳይሰማ ይኸው ዛሬ ላይ ደርሰናል … አሁን ላይ ግን ምን ጉድ እንደገጠመን ከአይምሮዬ በላይ ሁኖብኛል፡፡ አባት ልጁ ሲያጠፋ መምከር ብቻ ሳይሆን ይቆነጥጠዋል ፣ ይገርፈዋል አረ እንደውም በርበሬም ያጥነዋል… ታዲያ ይህ መልካም ባህላችን ዛሬ ላይ ማን ይሆን የቀማን? ጌታ መድሃንያለም ብቻ በቸርነቱ እንዳይለየን አጥብቀን መፀለይ ያለብን ሰዓት ቢኖር የአሁኑ ነው፡፡ ዳኒም በዚህ ውዝንብር ሰዓት ላይ የት ሂጄ ልጠይቅ የት ሂጄ ይውጣልኝ በምልበት ሰዓት ላይ ልቤን ያስደሰተኝና ከልቡ አንብቦ ለሚረዳውና ለሚማርበት ታላቅ ምክር የሆነውን ፅሁፍ ስለፃፍክልን አሁን ካለህ ፀጋ በላይ አብዝቶ ረጅም እድሜና ጤና ሰጥቶ እነድያቆይህ ምኞቴ ነው፡፡
ReplyDeleteወስብሐት ለእግዚአብሄር !!!
It seems Jesuses preaching and having of prediction for those who try to make our churches empty.Dany this is an amazing hand that wrote to pay whatever problem comes from anywhere.We pray all the time God to be with you.DDT Gola Michael S.S
ReplyDeleteTekatelin min enehun min enaderg egna memenan bemin enagez???
ReplyDeleteI was discussing with my wife and my five years old child to visit the exhibition, I couldn't believe this has actually happened. Ke'abune paulos enkuan ayimarum - esachew begid teyizew befetari tegelelu. Sew yaw sew new. Sanawkew Tehadisowoch eyemerun yihon, cheru medhanialem hoy ebakih tolo siman, atizegy. Orthodoksawinet ena ethiopiawinet mezebabecha honew aykerum. Lezih lememot yetezegaju millionoch aluna. " Endesemanew Endezihu Ayen". Min madreg endalebin ebakachihu nigerun.
ReplyDeleteAbetu Maren Eskemeche Titalanaleh, Abetu Beka Belen, Temelesilin, Egnam enimelesalen. Ethiopian Yikir belat, Sile enatih bileh, silalefut siledegagochu bileh, Ezenilin Raralin, Fikir Siten. Aderahin Yeminiwodeh Medhanialem Hoy Lenufake ena Lemenafikan Asalifeh Atisten. Amen
ReplyDeleteከአባ ጳውሎስ የባሱ የከፉ ቤተክርስቲያንን አዋኪ የሆኑ ፓትርያርክ መሆናቸውን እያየን ያለበት ሁኔታ ነው ያለው።
ReplyDeleteEWUNET NEW
ReplyDeleteሌላውን ስትገመግም አንተ በውጭ ያለውን ቤተክርስቲያን እነደ ሌላ አድርገህ ሌሎችን ከእናት ቤተክርስቲያን እያልክ ልዩነት እየፈጠርክ ሀይማኖትን ባትከፍል እግዛብሄር ልቦና ይስጥህ። አባቶች ተለያዩ እንጅ እምነታችነ የቀደምቲቱ ንፅህት የሆነችው የኢትዬጰያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ አማኞች ነን። ከማስተማርህ በፊት ልብህን አንፃ።
ReplyDeleteማነው ከዚህ ሁሉ ጀርባ ያለው?
ReplyDeleteቤተ ክርስቲያንን በመዝረፍና በማዘረፍ ላይ በተሠማሩ ሙሰኞች ከኋላቸው የሚገፉት ፓትርያርክ አባ ማቲያስ የችግሩ ሁሉ ምንጭ አድርጎ መደምደም የብዙኃን ግምት ሊሆን ይችላል። ፓትርያርኩ ደብዳቤዎችን ከመፈረም፥ የሚናገሩት ነገር ተነግሮአቸው ስላልመረመሩትና መረጃ እንዲቀርብላቸው እንኳ ስላልጠየቁት ጉዳይ ካለምንም ይሉኝታ በየመድረኩ ከመናገር ያለፈ ምንም ድርሻ የላቸውም። ፖትርያርኩ ከተወሳሰበው የቤተ ክህነት አሠራር ለዘመናት ርቀው የኖሩ በመሆናቸው፣ ከትምህርት ዝግጅታቸውም አንጻር እየተደረገ ያለውን ነገር ለመረዳት በእጅጉ የሚቸገሩ በመሆናቸው እንደዚህ ያለውን የተጠና እና ከፍተኛ ጥንቃቄ የተደረገበትን ሁኔታ ለመምራት አቅሙም ሆነ ፍላጎቱ እንደሌላቸው ይታወቃል። ምንም እንኳ ሁሉም የሚሆነው በእግዚአብሔር ፍቃድ ነው ብሎ ራስን መሸንገል ቢቻልም፣ የተመረጡበትን ሁኔታ፣ ከተመረጡም በኋላ የነበራቸው በጎ እቅዶች በፍጥነት እንዴት እንደተቀለበሱ ለሚረዱ የቤተ ክርስቲያኒቱ ልጆች ፓትርያርኩ እንዲፈጽሙት የተሰጣቸውን ተልዕኮ ከመፈጸም ውጭ እየሰሩ ያሉት ነገር የለም። ስለሆነም የሌሎች ክፋት ማስፈጸሚያ መሣሪያ በመሆናቸው በተሰጣቸው መክሊት ብዛት እና ባላቸው ከፍተኛ ኃላፊነት ምክንያት ከተጠያቂነት የማያመልጡ ቢሆንም እርሳቸውን በመውቀስና በመርገም የሚገኝ ነገር ባለመኖሩ እንደሀገራችን ገበሬ “እዚያው ማርልኝ ያንን... " ብለን ብናልፋቸው ሳይሻል አይቀርም። በአዲስ አበባ ሀገረ ስብከት ግርግር እየፈጠሩና የፖለቲካ ታማኝነታቸውን የቤተ ክርስቲያንን ሀብት ለመዘረፍ የሚጠቀሙበትንም ከማንኛውም ተራ ወንበዴ የማይለዩትን ሙሰኞችም ለጊዜው ልንተዋቸው እንችላለን።
ነገሩን በሚገባ የምንረዳው ባለፈው ሩብ ምዕተ ዓመት ቤተ ክርስቲያንን ከተቻለ ህልውናዋን ማሳጣት፣ ያለበለዚያም በተከታታይ በሚተገበሩ ሥልቶች የማዳከም ዕቅድ ተይዞ ካለማቋረጥ እየተሠራ መሆኑን ስንመረምር ነው። ኢትዮጵያዊያን ሁልጊዜም የሚቀለንና በቀላሉ ትኩረታችንን የሚስበው የውጭ ኃይሎች ተጽእኖ አንድም በሥራ እንጂ ደጋግመን ስላወራነው ልናስቀረው የማንችለው በመሆኑ ደግሞም የከፋውንና ሊውጠን የቀረበውን የውስጥ ችግራችንን ከማየት የሚያዘናጋን በመሆኑ ለጊዜው እናቆየውና ወደ ውስጣችን ችግር እንመልከት። ላለፉት 23 ዓመታት የሀገራችንን መንበረ መንግሥት የተቆጣጠረው የፖለቲካ ኃይል ከመነሻው ዓላማዎቹን ለማስፈጸም እንደ እንቅፋት የሚቆጥራት የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ቤተ ክርስቲያንን በመደብ ጠላትነት ፈርጆ እንደሚሠራ ቋሚ መረጃ የሚሆነው የዶ/ር አረጋዊ በርሄ የዶክተሬት ዲግሪ ማሟያ ጽሑፍ ነው።
ለዚህ ማሳያው ድርጅቱ ሀገሪቱን በተቆጣጠረበት ማግስት የቤተ ክርስቲያኒቱን 4ኛ ፓትርያርክ በተለመደ መሠሪ አካሄዱ ከመንበራቸው ሲያባርር (ቤተክህነቱ ሁሌም ተሸክሞት የሚኖረው ውስጣዊ የአሰራር ዝርክርክነትና የዘር ሽኩቻ ተጨምሮበት) የነበረበትን ሥጋት በቀላሉ መረዳት ይቻላል (የቀድሞውን ምክትል ጠቅላይ ሚንስትር ታምራት ላይኔን ምስክርነት ያስታውሷል)። ገሚሱ በተለመደው የቤተክሀነቱ የውስጥ ሽኩቻ ለማትረፍ ሌላው ደግሞ በተጠናወተን “እኔ ምን አገባኝ” ጉዳዩ እንደቀላል ታይቶ ዝም ተባለ። ቤተ ክርስቲያን በአደባባይ የተደፈረችው ያኔ ነው።
ቤተክሀነቱ ኢህአዴግ ሀገሪቱን ሲቆጣጠር የተሻለ አቅምና ጥብዓት ያላቸው ሊቃነ ጳጳሳትና ሊቃውንት እንደነበሩት ባይጠረጠርም ከዚያ ወዲህ ግን ምንም ፍሬ እንዳያፈራ ከፍተኛ የማዳከም ዘመቻ ተከፍቶበታል። ኢህአዴግ በወቅቱ በተፈጠረው ግርግር በግላቸው በነበራቸው ከፍተኛ የመግባባት ችሎታና በላቀ የትምህርት ደረጃቸው ሁኔታውን ለማዘናጋት የተመቹትን ብጹዕ ወቅዱስ አቡነ ጳውሎስን በቀላሉ ወደ መንበሩ አመጣቸው። ከዚያም በትምህርተ ሃይማኖት ጽኑአን እና በምግባራቸው የሚታወቁ ሊቃውንተ ቤተ ክርስቲያንን እና ሊቃነ ጳጳሳትን በተለያየ ዘዴ በማዳከም በተጠናና በብዙ ዝግጅት የቤተ ክርስቲያኗን መዋቅር እንዲቆጣጠሩ ከበረሃ ጀምረው በሰለጠኑ “መነኮሳት” እና ጥቁር ራሶች የቤተ ክርስቲያኒቱ መዋቅር ከሀገር እስከ ውጭ ሀገር እንዲያዝ አደረገ። አሁንም ከእነዚህ ታማኝ የፖለቲካ ስልጡኖች ጥቂት የማይባሉትን ወደ ጵጵስና ማዕረግ ለማድረስ ከፍተኛ ጥረት እያደረገ ነው። እውነተኞቹ አገልጋዮች እየተገፉ በተከበረው በምንኩስና ስም የቤተ ክርስቲያንን ሀብት የሚዘርፉና ተቀዳሚ ዓላማቸው የፖለቲካ መሳሪያነት የሆኑ ካድሬዎች ቆብ እያጠለቁ በወሳኝ መዋቅሮች ጭምር በኃላፊነት እንዲቀመጡ አደረገ። እነዚህ አካላት ከሀገር ቤት እስከ አሜሪካ በተዘረጋ ሰንሰለት ቤተ ክርስቲያንን ከሚዋጉ ከሁሉም አካላት ጋር እየመከሩ ቤተ ክርስቲያንን የማዋረድና ዓላማዋን የማደናቀፍ ሥራቸውን በፖለቲካው ሙሉ ድጋፍ እያከነዋኑ ይገኛሉ።
ይህም አልበቃ ብሎ ነብሰ በላ የሚባለው ደርግ እንኳን (የሚከተለው የማርክሲዝም ሌኒኒዝም ርዕዮት “ቢፈቅድለትም”) እየፈራ እየተባ የሚያደርገውን ቤተ ክርስቲያንን እና አባቶችን የመዳፈር ተግባር ገዢው ፓርቲ ካላምንም ፍራቻ (ምንም የፖለቲካ ኪሣራ እንደማያስከትል በማስላት) ገፋበት። የኢህአዴግ ባለስልጣናት ካለምንም ግብዣ ወደ ቤተክህነቱ በፈለጉበት ቀንና ሰዓት እየመጡ (ካላደረሳቸውም በስልክ) ለፓትርያርኩና ለሊቃነ ጳጳሳቱ መመሪያ እስከመስጠት ደረሱ። ሊቃነ ጳጳሳትን የሚደበድቡና የሚያስፈራሩ የቤተክህነት “ደህንነቶችም” ተፈጠሩ። ማንም የእነሱን ዘረፋ ለማስቆም የሚሞክር ቢገኝ የፈለጉትን ለማድረግ ሙሉ የመንግስት ድጋፍ እንዳላቸው በአደባባይ የሚናገሩና፣ ሲፈልጉም የተቃወማቸውን ሁሉ በወታደር እያስገፉ ከእስር ቤት መጨመር የሚችሉ የቤተክህነት “ባለሥልጣናት” ተፈጠሩ።
ይህ ሁሉ በቤተ ክርስቲያን ላይ እየደረሰ ባለበት ሁኔታ ራሱን ከአደጋ ለመጠበቅ የተለያዩ ጥበቦችን እየተጠቀመ የዘለቀ (ብዙዎች ፍራቻ ነው ቢሉትም) ነገር ግን በቤተ ክርስቲያንና በሀገር ላይ ቀላል የማይባል አዎንታዊ ለውጥ እያመጣ ባለው ማኅበረ ቅዱሳን የተዘጋጀው የቤተ ክርስቲያን መርሐ ግብር እንዲስተጓጎል መደረጉ መታየት ያለበት በዚህ ዐውድ ነው።
nice view
Deleteቀሲስ የ“ክብረት ልጅ”፥ ምነው በስድብ ቃል በጣም ጮኸ?!
ReplyDeleteየክብረት ልጅ እይታዎቹን በሚያቀርብበት ብሎጉ፥ “ፓትርያርኩ፦ ለኢትዮጲያ የደኅንነት ፣ ለምእመናን የድኅነት ሥጋት” በሚል አንድ ጽሁፍ፥ ዛሬ አስነብቦ ድንገት ያየ ሰው ጠቆመኝና ወደጡመራው መድረኩ ገብቼ አነበብኩት፡፡ ዳንኤል በዚህ ጽሁፉ “100% ማኅበረ ቅዱሳን ሊያዘጋጀው ከጫፍ የደረሰውን ዐውደ ርእይ የከለከሉት ፤ ያስከለከሉት ፓትርያርኩ ናቸው”፥ ብሎ ደምድሞ አስቀምጦታል፡፡ የዐውደ ርእዩ ባለቤት ማኅበረ ቅዱሳን ደግሞ፥ በዋናው ጸሐፊው አቶ ተስፋዬ ቢኾነኝ በኩል ትላንት ማምሻውን ለጋዜጠኞች በሰጠው ጋዜጣዊ “መግለጫ”፥ “ለመታገዱ ፓትርያርኩ እንደሌሉበትና በመንግሥት አካላት መመሪያ መታገዱን”ይፋዊ መግለጫ ሰጥቷል፡፡
ዳንኤል ፓትርያርኩን ከሰይጣን እኩል ነበር የሳላቸው ፤ “... ፓትርያርክ ማለት በግሪክ “ታላቅ አባት” ማለት ነው፡፡ የታላቅ አባት ተግባር የልጆቹን ሥራ ማፍረስ አይደለም ፤ ለዚህማ አባት አያስፈልግም ሰይጣን እንጂ፤ ...” በማለት፡፡ እንደከዚህ ቀደም ልማዱ ዳንኤል ሌሎች ማስጮኺያዎችንም በዚህ ጽሁፍ ለማካተት ጥሯል፡፡ አዳዲስ ስድቦችንም ለፓትርያርኩ እንደእጅ መንሻ አቅርቦላቸዋል፡፡
ቅዱስ ቃሉ ግን እንዲህ ይላል፥ “ፈራጆችን አትስደብ፥ የሕዝብህንም አለቃ አትርገመው።” (ዘጸ.22፥28) የሕዝብ አለቃ ወይም መሪ የሆነ ገዥ በምድር ላይ የእግዚአብሔር ተወካይ ፤ እንደራሴም ነው፡፡ ስለዚህ ልናከብረው ፤ በመውደድም ከሁሉ በፊት ልንጸልይለት ይገባል፡፡ ቅዱስ ጳውሎስ ሳያስበው ይህን ቃል በመተላለፉ ምክንያት ወዲያው ተጸጽቶ ተመለሰ ፤ አለማስተዋሉንም ተናገረ፡፡ (ሐዋ.23፥4-5) ፍትሐ ነገሥቱም “በእነርሱ ላይ የተሾመውን ጳጳስ ... እንደትልቅ ወንድም ያክብሩት መሪና አስተዳዳሪ እንደመሆኑ መጠን ሊታዘዙለት ይገባል” ይላል፡፡ (አን.4 ቁ.53) ዳኒ! ይህ የሕግ ቃል አንተን አይመለከትም ይሆን?!
የቤተ ክርስቲያን የቀኖና መጽሐፍ ፍትሐ ነገሥት በአንቀጽ.6 ስለቀሳውስት ድርሻ ባሰፈረበትና ቀሳውስት ከማዕረገ ክህነታቸው ስለሚሻሩበት ሁኔታ ሲዘረዝር “... ሕግን አውቆ የማይሠራባት ... ቄስ ይሻር፡፡” በማለት በግልጥ ያስቀምጣል፡፡ ዳኒ! እንኳን መንፈሳዊውን ሥጋዊውን የዚህን አለም ምድራዊ ሕግ መጣስህን አውቀኸዋል? ማኅበሩ ፓትርያርኩ አልከለከሉኝም እያለ፥ አንተ ግን ለፓትርያርኩ የስም ማጥፋት ዘመቻ ከፍተሃል፡፡ እንደቤተ ክርስቲያን ቀኖና ከቅስናህ ትሻር ይሆን? እውነታው ግን አይመስልም፡፡
ፓትርያርኩ ቢያጠፉ እንኳ የቤተ ክርስቲያን ቀኖና ምን ነበር የሚለው? ጅል ፣ ሰይጣን ፣ የክፋት አነሳሽ ... እያሉ በአደባባይ ፓትርያርክን መዘርጠጥ አለበት የሚል “ቀኖና” አለን?! ለመሆኑ ስድብ ከማን ነው? የሕዝብን አለቃ አለማክበርስ? ያንን ሁሉ መጽሐፍ የጻፈው “ደራሲና ተመራማሪ” ምነው ምራቅ እንዳልዋጠ “ፍንዳታ”(የቀድሞው ጠቅላይ ሚኒስቴራችን ቃል ናት) ደርሶ ቱግ አለ?! እንዴ ይህ ነበር እንዴ በውስጡ የነበረው?!
ውድ ወንድሜ ቀሲስ ዳንኤል፦ ቤተ ክርስቲያን ቀኖና አላት ፤ በየትኛውም የቤተ ክርስቲያናችን ቀኖና ሽቅብ ፓትርያርክን እንዲህ መዘርጠጥ አይደለም ምእመንን መናገር አጸያፊ ነው፡፡ ተግሳጽ ነው ብትለኝ፥ ለመሆኑ ተግሳጽ መቼ ነው የሚመጣው? ደርሰህ ከመገሰጽህ በፊት ስንቴ ይሆን የመከርካቸው? ስንቴ ይሆን የወቀስካቸው? ስንቴ ይሆን ካሉበት ነቀፌታ እንዲርቁ በሚራራ ልብ አዝነህላቸው እንደእግዚአብሔር ቃል በጸሎት ቃል ወደጌታ የማለድክላቸው? ... ደጋፊ ስላገኙ ብቻ ብዙ ማለት፥ ከማያዳላ ኅሊና ጋር ያፋጥጣል፡፡ ወንድምን ሰባት ጊዜ ሰባ ይቅር ማለትና መቀበል እኮ ከአባት ባሻገር ወንድም ለሚሆነን ፓትርያርክንም ያካትታል ፤ ለመሆኑ ይህን ታውቀዋለህን?!
ፓትርያርኩ ቢያጠፉ ቤተ ክርስቲያን ቀኖና አላት፡፡ “...የአገሩ ሁሉ ኤጲስ ቆጶሳት ስለእርሱ የሚገባውን ይመረምሩ ዘንድ እርሱንም ለማየት በየዓመቱ ሁለት ጊዜ ከጳጳሳቸው (ፓትርያርካቸው) ዘንድ ይሰብሰቡ፡፡ ስለተሰጣቸው ሥልጣን በምታስፈራዪቱ ቀን መልሳቸው የጸናች ትሆን ዘንድ፡፡” (አን.4 ቁ.55) የሚል፡፡ የሚያዩት ፊቱን ብቻ አይደለም ፤ ሥራውን በማየት ያመሰግኑታል ፤ ነቀፌታም ካለ ይነቅፉታል፡፡ ዳኒ! ይህችን አላነበብካት ይሆን?! ፓትርያርኩን መውቀስና መምከር ፤ መገሰጽም ካለብህ መንገዱን አልሳትከው ይሆን? ይህን ያህል ግን ለምን ይሆን የጠላሃቸው? ዳኒ! ወንድምን ስለመጥላት ቃሉ በትክክል ይወቅስሃል፡፡
በእርግጥ ዳንኤልና ማኅበሩ መንገድ ሲተላለፉ ይህ የመጀመርያው አይደለም፡፡ ግን እውነት ለመናገር ባልተጣራ ወሬ ፤ በተራ አሉባልታ ያውም ስንት ሽልማት ያግበሰበሰው ሰው ይቺን ትንሿን ነገር ከማጣራት ቸኩሎ “በሚቆረቆርላት” ቤተ ክርስቲያን መሪ ላይ የስድብ ናዳ ያወርዳል ብሎ ማን ይጠብቃል?! ከዚህ ስህተቱ ይማር ይሆን ዳንኤል? ወይስ ወደፊትም ሌላ የስድብና የመዘርጠጥ ጽሁፍ ያስነብበን ይሆን? ወይስ እንደጳውሎስ በግልጥ የይቅርታ ልብ ይዞ “የሕዝብን አለቃ” ስለተሳደበበት ስድቡ ንስሐ ይገባ ይሆን? የምናየው ይሆናል፡፡ ፈጥነህ ንስሐ ብትገባ ግን ማሰናከያን ታስወግዳለህና እስኪ ቀድመህ ወደራስህ እይ!!!
ጌታ ማስተዋሉን ያብዛልን፡፡ አሜን፡፡
At first I want to appreciate your patient comment. I believe this is the way that we can learn each other.
DeleteSecond my comments on you
1. ቅዱስ ጳውሎስ ሳያስበው ይህን ቃል በመተላለፉ ምክንያት ወዲያው ተጸጽቶ ተመለሰ ፤ አለማስተዋሉንም ተናገረ
You better also read the bible thoroughly. It did not say with out his mind, it says unknowingly. Besides what st. Paul did after that has an implication on his deliberate words.
2. How much did you search that Dn Daniel have tried to tell the Patriarch.
I think you are based on your feelings. Besides as you know the door of the Pope is closed for such a person. But as far as a read from his blong he has done it several times. If your comment is , is he the right person for that??. My answer is no but some times you do things knowingly that it is wrong.
3. I never heard Dn Daniel becomes Kesis. You better ask some body.
4. The official statement of the MK secretary and Dn Daniel kibret's say is not different. Daniel did not say directly the Exhibition is canceled by the Pope. Instead he say the back is the Pope.
5. You said that "why you abominate the Pope like this irrespective of the bible say". Do not you have read that Peter the apostle has killed Hananiya and Sepira. Abominate and admonition are different.
Any ways I like your approach...
ደጋፊ ስላገኙ ብቻ ብዙ ማለት፥ ከማያዳላ ኅሊና ጋር ያፋጥጣል፡፡
Deleteወንድሜ የሚያስተውል ልቦና ካለው እጅግ ውብ የሆነ ምክር ነው የለገስክለት መጠቀም አለ መጠቀመ የርሱ ፈንታ ሆኖ
Deleteቅዱስ አባት በንደዚህ አይነት መድፈር መሳደብ አይገባም ነበር ላንተ ግን እግዚአብሔር እድሜህ ያርዝመው አመሰግናለሁ
ለሚሰማም ለማይሰማም እንዲህ ከ ስርዓት የወጣ አነጋገርም ይሁን ጽሁፍ ሲደርስህ በንደዚህ መልኩ በሚያስተምር አገላለጥ ብታቀርብ ጥሩ ይመስለኛል
ውድ ወንድሜ ቀሲስ ዳንኤል፦ ቤተ ክርስቲያን ቀኖና አላት ፤ በየትኛውም የቤተ ክርስቲያናችን ቀኖና ሽቅብ ፓትርያርክን እንዲህ መዘርጠጥ አይደለም ምእመንን መናገር አጸያፊ ነው፡፡ ተግሳጽ ነው ብትለኝ፥ ለመሆኑ ተግሳጽ መቼ ነው የሚመጣው? ደርሰህ ከመገሰጽህ በፊት ስንቴ ይሆን የመከርካቸው? ስንቴ ይሆን የወቀስካቸው? ስንቴ ይሆን ካሉበት ነቀፌታ እንዲርቁ በሚራራ ልብ አዝነህላቸው እንደእግዚአብሔር ቃል በጸሎት ቃል ወደጌታ የማለድክላቸው? ... ደጋፊ ስላገኙ ብቻ ብዙ ማለት፥ ከማያዳላ ኅሊና ጋር ያፋጥጣል፡፡ጌታ ማስተዋሉን ያብዛልን፡፡ አሜን፡
Deleteውድ ወንድሜ ቀሲስ ዳንኤል፦ ቤተ ክርስቲያን ቀኖና አላት ፤ በየትኛውም የቤተ ክርስቲያናችን ቀኖና ሽቅብ ፓትርያርክን እንዲህ መዘርጠጥ አይደለም ምእመንን መናገር አጸያፊ ነው፡፡ ተግሳጽ ነው ብትለኝ፥ ለመሆኑ ተግሳጽ መቼ ነው የሚመጣው? ደርሰህ ከመገሰጽህ በፊት ስንቴ ይሆን የመከርካቸው? ስንቴ ይሆን የወቀስካቸው? ስንቴ ይሆን ካሉበት ነቀፌታ እንዲርቁ በሚራራ ልብ አዝነህላቸው እንደእግዚአብሔር ቃል በጸሎት ቃል ወደጌታ የማለድክላቸው? ... ደጋፊ ስላገኙ ብቻ ብዙ ማለት፥ ከማያዳላ ኅሊና ጋር ያፋጥጣል፡፡ጌታ ማስተዋሉን ያብዛልን፡፡ አሜን፡
Deleteይድፋህ አቦ ተንኮለኛና ክፉ ነህ
ReplyDeleteመድሃኔ ዓለም እድሜህን ያርዝመዉ፡፡መድሃኔ ዓለም እድሜህን ያርዝመዉ፡፡
ReplyDeleteIt is a diabolic war to hear and see this during this fasting period. The church and the leaders should have been the preachers not the blockers. God will see and will pay them back. I do not think they are spiritual at all. The exhibition will be seen invisibly to strengthen the faith of orthodox.Christians will hear it than they would have seen it.
ReplyDeleteበሀገሪቱ ላይ የነገሠው ኢ-ሰባአዊነት፤ ሕገወጥነት፤ ዴዴብነት (በሀገሬ ዘይቤ) እና ግርግር ፈጣሪነት እሰካልተወገደ ድረስ ሰላም አናገኝም!!!!!!
ReplyDeleteEndeh Fet ayto yemayadala tsehafe ayasatan.
ReplyDeleteDear D/n Daniel: Qale Hi'ywot yasemalin!
ReplyDeleteThis is one great article - for the one who can listen. But, please be careful, the govt and church officials will not hesitate to take you out if they decide you are a danger, just remember.
ድንቅ ነው ልክ ነው ዝምያለ ሁሉ የሞተ የሚመስለ አለ። ዛሬ ዘመናችን እጅግ የረቀቀ የፈጠነም ነው ይህም ለዚህ ለረቀቀና ልከፋ የክርስቶስ ተቃዋሚዎች ቁልጭ አድርጎ ለማሳወቅ የተሰራ ነው ስለሆነም ጸረክርስቶሶች ይህ ዘመን ለእነርሱ ስውር ጥፋት መገለጫ መታወቂያ መሆኑ ሳይሆን መስሎ የታያቸው በጥፋት መንበር ላይ መቀመጣቸው አንድ ሰይጣን አፎሚያን ሊያስታት ይማጥፊያውን በትር ብሎም ላራሱ ማጥፊ ቅዱስ ሚካኤል ነኝ ብሎ ለዚያች ቅጽበታዊ ጊዜ የሚያስታት መስሎት የጥፋት የሀሰት የማወናበድ ቃላቱን አንደዚሁ አንደ ዛሬው ሞከረ። ነገር ግን እውነተኛው መላእክ ቅዱስ ሚካኤል በጊዜው ጊዜ እውነቱን ገልጾ ከነበረበት አጥፍቶታል። ይገርማል ይህም እኮ አለ አንክዋን የዚህች የምትጠፋ ምድር ስልጣ። ኧረ በክብር ማለፍ ጽድቅ ነው አባቶች!!!!!
ReplyDeleteበጣም የሚያሳዝን ስራ ነው እየተሰራ ያለው፣ከወራት በፊት በዚህ በእንግሊዝ ማንቸስተር የስላሴ ቤተክርስቲያን በተፈጠረው የቤተክርስቲያኒቱ ችግር ቅዱስ ሲናዶሱ ለተላከለት ደብዳቤ መልስ ባለመስጠቱ አሳዝኖናል፣ በዚህም ጉዳይ ወንድሜ ዳንኤል አጫውቸህ ነበር አሁንም የቤተክርስቲያኒቱ ቀኖና ፣ሰርዓት ሲፈርስ የምናየው በሃይማኖት አባቶቻችን። ይህ እስከመቸ ይሆናል።
ReplyDelete"፳፰ - አሁንም በገዛ ደሙ የዋጃትን የእግዚአብሔርን ቤተ ክርስቲያን ትጠብቁ ዘንድ መንፈስ ቅዱስ እናንተን ጳጳሳት አድርጎ ለሾመባት ለመንጋው ሁሉና ለራሳቸሁ ተጠንቀቁ ።"
ReplyDeleteየሐ.ሥራ ፳፥ ፳፰
እግዚአብሔር ይስጥህ ፤ ለሚያስተውል ዛሬም እግዚአብሔር ለታላላቆቹ በልጆች አንደበት ይናገራል።
ወንድሜ ፦ዕድሜ ከጤና ሰጥቶ ፣ በቅድስት ተዋሕዶ ሃይማኖት አጽንቶ ፤ ጸጋውን ያትረፍርፍልህ ።
‹ከክምር ድንጋይ ላይ ይበቅላል ደደኾ
ReplyDeleteየፈራሁት ነገር መጣ ድኾ ድኾ›
የገዛ ፓትርያርካችን ለእኛ ለምእመናን ድኅነትን እንዳናገኝ ሥጋት ሆነውብናል፡፡ የታገሡትን ሁሉ ለክፋት በማነሣሣት ደግሞ ለሀገሪቱ ደኅንነት ሥጋት እየሆኑ ነው፡፡
ReplyDeleteእግዚአብሔር መሻያውን ያምጣ እንጂ ቤተክርስቲያናችን ያለችበት ሁኔታ ከመቼውም ግዜ ጋር በማይመዛዘን ከፍተኛ አደጋ ውስጥ ናት። ምቼም የአባቶቻችን አምላክ አሳልፎ አይሰጣትም
ReplyDeleteየማይገሠፅ ፓትርያርክ የለንም !
ReplyDelete(ርዕሱን የተጠቀምኩት ፥ በፌስቡክ ከአንድ የሌላ ሰው ጽሑፍ ሥር ከተሰጠ አስተያየት ቀጥታ በመውሰድ የራሴን ሐሳብ ለማብራራት ተመራጭ ሆኖ ስላገኘሁት ነው)
ፓትርያርኩ ሮምን ጎብኝተው በተመለሡ ማግሥት ጀሌዎቻቸው ተሰበሰቡና " ማኅበረ ቅዱሳን ፓትርያርኩን ይቅርታ ይጠይቅ " አሉ ። ቀደም ብለው እኝህ ሰው አባ ማትያድ " ከካቶሊክ ጋር የሰፋ ልዩነት የለንም ፤ ልዩነታችን ጠባብ ነው " ማለታቸውን ልብ ላለ ሰው እና የጀሌዎቻቸው "ይቅርታ ይጠየቁ " ምክር የአንድ ሣንቲም ሁለት ገፅታ ትርጉም ይዞ እናገኘዋለን ።
ሲጀመር እኛን ኦርቶዶክሳውያንና እነዛን ካቶሊካውያን አንድ የሚያደርገን የሃይማኖት ትምህርት የቱ ነውና ነው " ከካቶሊክ ጋር የሰፋ ልዩነት የለንም ፤ ልዩነታችን ጠባብ ነው " የምንባለው ?!
ባይሆን ፦ ሆዳቸው እንደ ባሕር የሰፋ ፣ አዕምሮአቸው እንደ መርፌ ቀዳዳ የጠበበ የፓትርያርኩ ጀሌዎች " ለፓትርያርኩ ደብዳቤ መጻፍና ሽቅብ እሳቸውን መናገር ስህተት ነው " አሉና " ማኅበረ ቅዱሳን ይቅርታ ሊጠይቅ ይገባዋል " በማለት ስፋትና ጥበት የሌለበትን የራሳቸውን ካቶሊካዊ አስተምህሮና እምነት ፥ ቀድሞ ፓትርያርኩ " ልዩነት የለንም " ሲሉ ፤ አጋፋሪዎቻቸው ደግሞ " እሳቸውን ማን ተናግሮ ?! " አሉና " ይቅርታ ይጠየቁ " በማለት የእምነት ጠርዛቸውን "ፓትርያርኩ የክርስቶስ እንደራሴ ነው ፤ የፓትርያርኩ ሁሉ ነገር ትክክል ነው " በሚለው የካቶሊክ ፈሊጥ ለክስ ተነሡ ።
አሁን ለእኔ ትርጉም የሰጠኝና ሰውም እንዲያስተውለው የወደድኩት የአባ ማትያድንም ሆነ የግብረ አበሮቻቸውን " ካቶሊክ ፣ ካቶሊክ " የሚሸት ተግባር ነው ። ለዚህም ነው የአንድ ሣንቲም ሁለት ገፅታ ትርጉም ይዞ እናገኘዋለን ያልኩት። እንጂ " መሰደብ አለባቸው (ምናልባት ተሰድበው ከሆነ ፥ ማኅበረ ቅዱሳን አልተሳደበም እንጂ) ፣ ይቅርታ መጠየቅ አያስፈልግም ... " ዓይነት ጉንጭ አልፋ ክርክር ውስጥ ለመግባት አይደለም ።
ሆኖም ግን የአባ ማትያድን " ከካቶሊክ ጋር ልዩነት የለንም " እና የጀሌዎቻቸውን " ይቅርታ ይጠየቁ " የሚለውን ምክንያተ ነገር በዚህ ጽሑፍ ልለፈውና " ፓትርያርክን ሽቅብ መናገር አይገባም ፤ ፓትርያርኩ የተናገረውና የሚያደርገው ሁሉ ትክክል ነው ፤ እሱ የክርስቶስ እንደራሴ ነው ፤ እርሱን መናገር ድፍረትና ስህተት ነው " የሚሉ ጨዋታዎች ላይ ጥቂት ነገርን ለማስገንዘብ ወድጃለሁ ።
ይኼም አስተሳሰብ በአንዳንድ የዋሃን ምዕመናን ዘንድም ሲነገር ስለምሰማ ነው ፦
- እሳቸው አባት ናቸው መታዘዝ አለባችሁ
- ያሏችሁን እሺ ብላችሁ ብቻ ተቀበሉ
- ፓትርያርኩን መናገር የለባችሁም
- እግዚአብሔር ነው የሾማቸው ( ቀልድ ¡ ... አላየንም አልሰማንም አሉ ሲሾሙ ¡ .... አስቀድሞ ሳጥናኤልን የሾመው ማን ነበር? ግብሩ ሌላ ሆነ እንጂ! ... ሳኦልን ንጉሠ እሥራኤል አድርጎ የሾመው ማነው? ... ውጤቱን አይተነዋል እንጂ! ... ይሁዳን ሐዋርያ ያደረገና እንዲያውም የማኅበረ ሐዋርያት ዐቃቤ ንዋይ /ገንዘብ ተቀባይና ሰብሳቢ/ አድርጎ የሾመው ማን ነበር? ... ሣንቲም ይሰርቅ ነበር እንጂ! ..... መሾሙንማ እግዚአብሔር ሾሟቸው ነበር ፤ ግን ተገስፀዋል ፤ ሽቅብም ተመክረዋል ። አልሰሙምና ተጥለዋል እንጂ )
፡
፡
፡
ወዘተርፈ .... " ፓትርያርኩን ሽቅብ ወጥታችሁ አትናገሩ " ዓይነት ሐሳቦችን እሰማለሁ ፤ በአንዳንዶቹ ተፅፈው አነባለሁ ፤ ጥቂቶቹም በአካል ስንገናኝ ተሟግተውኛል ።
አንድ ጥያቄ አለኝ !
የሃይማኖታችን የበላይ ማነው ?
መልስ ፦
ለእኔ የሃይማኖት የበላይ የማመልከው እግዚአብሔር እንጂ የሃይማኖቴ የበላይ ፓትርያርኩ ወይ ጳጳሱ አይደለም ።
ፓትርያርኩ ወይም ጳጳሱ የሃይማኖት የበላይ ሳይሆን የቤተ ክርስቲያኗ የክህነት ወይም የሹመት የበላይ ነው ። ያውም የክህነት እንጂ የአስተዳደር እንኳ አይደለም ። የቤተ ክርስቲያናችን የአስተዳደር የበላይ ቅዱስ ሲኖዶስና ቅዱስ ሲኖዶስ ብቻ ነው። ቤተ ክርስቲያንን የሚመራትና የሚያስተዳድራት እግዚአብሔር መንፈስ ቅዱስ ቢሆንም እውነቱ ፥ በዚህ እውነት ላይ የተመሠረተ ቅዱስ ሲኖዶስ ቤተ ክርስቲያንን ያስተዳድራታል ።
በዚህ መንፈሰሳዊ አስተዳደር ውስጥ ፓትርያርኩም ሆነ ጳጳሱ የተሰጠው ተግባርና ኃላፊነት ያለውና የተሾመውም ይህን አስተዳደራዊና ክህነታዊ መንፈሳዊ ተግባር እንደሃይማኖቱ ዶግማና ቀኖና በመፈፀም መንጋውን የሚጠብቅና የሚያሰማራ ነው እንጂ .... የሃይማኖቴ የበላይ አይደለም ። እኔም ሆንኩ እንደእኔ ያለ አንድ ተራ ምዕመንና ጳጳሱ ወይም ፓትርያርኩ በሃይማኖት ፊት እኩል ነን።
ግሩም አገላለጽ ፤ በሃሳብ እስማማለሁ ወዳጄ ።
DeleteDN.Daniel Egzeabher yeredan zend ye kidusanu teshlote yasfelgenenal Daniel anten gen Daneilen ke anbesesoche mengaga ye tadege Amlak antenem yetadeghe.
ReplyDeleteየማኅበሩ አመራርም ቢሆን ጊዜውን አይቶ የሚሣለጥ አመራር እንጂ የተቸከለ አመራር መሆን የለበትም፡፡ የፓትርያርክ ማትያስ ዘመን እንደ ፓትርያርክ ጳውሎስ፣ የጠቅላይ ሚኒስትር ኃይለ ማርያምም ዘመን እንደ ጠቅላይ ሚኒስትር መለስ አይደለም፡፡ አሁን የሆነው ነገር ሊሆን እንደሚችል ቀድሞ እየታወቀ ከግንቡ ጋር እስኪጋጩ ድረስ ቆሞ መጠበቅ ብልህነት አይደለም፡፡ አሁንም ‹እገሌ የተባለ ባለሥልጣንን አናግረናል፤ እገሌ የተባሉ አባት አይዟችሁ ብለውናል› እያሉ መጓዝ የሚያዋጣ አይደለም፡፡ ለጉባኤ ተሰብስቦ ‹ ለፓትርያርኩ የተጻፈው ደብዳቤ አንጀት አርስ ነው› ብሎ አጨብጭቦ የሚበተን አመራር ጊዜው ሊያልፍበት ይገባል፡፡ ከዲሚትሪ ሆቴል እስከ ፌዴራል ጉዳዮች የተደረጉትን ውይይቶች ገምግሞ አዲስ አቅጣጫ መያዝ ይገባ ነበር፡፡ የሚሰበሰብ ብቻ ሳይሆን የሚተነብይ አመራርም ያስፈልጋል፤ ካልሆነ ግን
ReplyDelete‹ከክምር ድንጋይ ላይ ይበቅላል ደደኾ
የፈራሁት ነገር መጣ ድኾ ድኾ› የተባለው ይደርሳል፡፡
Kale hiywet yesemalin Deacon Daniel
ReplyDeleteመምህር ሆይ በእጅጉ አዘንኩብዎ
ReplyDelete+ በብዙ ሚዛን የሳተ ፤ በብዙ ከርስዎ የማይጠበቅ ፤ በብዙ ድፍረትና ንቀት የተሞላበት እንዲህ ያለ አስተያየት ከእርስዎ አልጠብቅም ነበር መንፈሳዊ ሚዛንዎን እንደሳቱ ግን ክዚህ ሌላ ማሳያ አያሻም ፡፡
+ ምንም ይሁን ምን እግዚአብሄር በሾመው ላይ ያውም በህይወት እያለ ቅዱስ ተብሎ የሚጠራውን አባት እንዲህ ባለ ንቀትና ስድብ ለሰዳቢ አሳልፎ መስጠት በእውነት ከርስዎ ይጥበቃል? ነው ወይንስ አለሙ በሰጠዎት ዝና ግር ተሰኝተው እራስዎን ከጵጵስና እና ከ ፕትርክና በላይ አደረጉ ይሆን?
+ አርዮስ እንካን ከሰይጣን ጋር ተነጻጽሮ አልተቀመጠም እንዲህ አንድ ፓትርያርክ የሚሰራውን ሰራ ከጠንቆይ አፍዝ አደንግዝ ጽሁፍ ጋር ለማነጻጸር እንዴት ድፍረቱን አገኙት መምህር? ምን ያለ ደገኛ አባትስ አስተማርዎ?
+ መምህር ሆይ እርስዎ እና የአላማ ወዳጆችዎ በግሩም ሁኔታ ከምትሰሩት አንዱና ዋናው አባቶቻችንን እንዳንሰማ ፡ እንድንንቅ ፡ አንዳንታዘዝ ብሎም አብረን እንድንሳደብ የምትስሩትን ስራ እናስተውላለን ፤ ይህም ደግሞ በነርሱ ላይ እምነት አትጠን በሌላው (-) እንድንታመን መንገዱን እየሰራችሁ እንደሆነ እረዳለሁ
+ ሁሉም በልዩልዩ ጸጋ አምላኩን ያገለግላል በዚህም እናንተ ቆማችሁ ሰታስተምሩ ብዙ የሄዳችሁ እኛ ቁጭ ብለን ስንማር ብዙ የቀረን አርጋችሁ አታስቡን በብዙ እናውቃለን አንዳንዴም እንቀድማለንና ማን ምን እንደሚሰራ ብቻ ሳይሆን እንደሚያስብም፡፡
+ ይሻል የነበረው እንደኔ እይታ እንደ ወትሮው ሁሉ አሁንም ዲፕሎማትነትዎን ተጠቅመው ወገንተኞችዎም ምነው ዝም አለ እንዳይሉዎት እግዚአብሄርና እኛ ደግሞ ምነው መምህር ሚዛናቸውን ሳቱ ብለን እንዳንቀየምዎት እንዲህ ካለው ጽርፈት ቢታቀቡ ነበር ወይንስ ቀድሞም የተሸፈነ ነገር ነበረዎ ?
+ ስለ ሁሉም ግን
ሀይማኖቱን እንተወውና በሀገራችን ሽማግሌ ይከበራል ሰይጣን ተብሎ አይሰደብም ወይንም ከሰይጣን አይነጻጸርም
ባልዋለበትም ከጠንቆይ አይነጻጸርም ሌላውን ብንተወው ፡፡
+ እንግዲህ ምን እላለሁ የበተኑትን መሰብሰብ እንዳይሆን አውቃለሁ ነገር ግን እግዚአብሄር ቢረዳዎ ልቦናዎ እሽ ቢልዎ ሽማግሌውን ይቅርታ ይጠይቁ የአባት እርግማን አጥንትን ትሰብራለችና !
ምነው አሻቅበህ እንዲህ አልከኝ ቢሉ ከመምህሬ ያገኘሁት ነውና እላለሁ!
አክባሪዎ birkneh from DALLAS USA
birknehheroda@yahoo.com
እርሳስና ላጲስ አብረው ይኖራሉ
Deleteግብራቸው ተቃርኖ የሚጽፈው ከታች
አጥፊው ከላይ ሆኖ '''
አይ ብርቅነህ፣ ደግሞ ክብር ይመስል ዳላስ ነው ያልሁት ትላለህ። ይኼኔ እኮ ወይ ታክሲ ሾፌር አልያም ጋዝ ስቴሽን ይሆናል ያለኸው።
Deletearif tsehuf new Dikon Daniel kebret, neger gen yehe guday ke patriyarku alefo lelam akal eji yalebet endehone geltse new, endene hasab ye illuminati agenda lemasfetsem yemidereg enkesekase yemeslegnal mekniyatum orthodoxn ende orthodox tagelew ena bezu mesewat kefelew yakomuwatn hayloch ende mehabere kidusan, memeher girma ena alu yemibalu abatoche lye yanetatere new .... gudayu betelk tayto kebad akuwam mewesed yalebet yemeslegnal
ReplyDeletehttps://www.facebook.com/yene.tes/videos/1190823977609275/
mn aynet adis hasab mns aynet tinbet metenbey neberebachew? mesrat endemenager siket endemaseb kelal bihon nuro eskahun snt neger betesera. hulum neger Amlak sifekd yihonal bilo mamens aygebam yihon? ye and neger alemefetsem hulu gize ye sew sihtet newn? sew yasbal Egziabher yifetsmal meche endet bale huneta new ende yemiseraw? ere enastewl. Dn daniel antes bebotaw bthon mn neber yemtadergew? ahun lalehbet dereja yaderesehn mahiber letewesenu sewoch bicha yenekah eyemeseleh batfetatenew melkam new. bante mkniat yetefeteru bizu negeroch lante mn aynet smet endemifetrlh alawkm. kom bleh maseb tegebi new. ye ametat sbketoch eko antenm yimeleketalu.
ReplyDeleteDani our microscope ! God bless you
ReplyDeleteዝምታ መቀበል፣ ሽንፈት የመሰላቸው ቤተ ክህደቱና ቤተ መንግሥቱ ውጤቱን እያደር ያዩታል፡፡ እኛም ጽዋዋ እስክትሞላ ድረስ መታገስ አያቅተንም፡፡ጽዋዋ የሞላች እለት ግን ….
ReplyDeleteቃለ ሕይወት ያሰማልን፡ በዚህ ጽሁፍ ኢይሀድጋ ለሀገር የሚለውን አይቸበታለሁ፡፡ ዘመነ ሰማዕታት …
እጅጉን የማከብርህ ወንደሜ ዲያቆን ዳንኤል ክብረት መቼም ይሄንን ጽሁፍ አንተ ነህ የጻፍከው ብሎ ማመን አቅቶኝ ለተወሰኑ ቀናት ከራሴ ጋ ታገልኩ
ReplyDeleteእኛ አባቶችን የሚሳደብ የሚንቅ የሚያዋርድ አስተማሪ አያስፈልገንም እሱንማ ያለአስተማሪ እያደረግነው አይደል ወንድሜ ዲያቆን ዳንኤል ፓትርያርክን ያክል ትልቅ አባት ባደባባይ ለመሳደብ ያበቃህ ሃይማኖተኛነትህ ይሁን ፖለቲከኛነትህ እሱን አንተው ታውቀዋለህ ›››
ለኔ እንደአንድ ክርስቲያን ካወራን ግን አንተው ካስተማርከው ትምህርት ላይ ልጥቀስልህ ሥልጣን ከእግዚአብሄር ነው “እንኳንስ ፓትርያርክነት ያለ እርሱ ፍቃድ የእንድ ቀበሌ ሃላፊ መሆን አይቻልም “ አየህ አንተ አስካሁን ዲያቆን ከሚለው ማዕረግ አልፈህ ስትሄድ አላየንም ታድያ የትኛው ያንተ ቅድስና የትኛው ጽድቅህ ነው ቅዱስ ፓትርያርኩን ሰይጣን ለማለት ያበቃህ ፡፡
ማህበረ ቅዱሳን አንተና ጓደኞችህ በቅን መንፈስ ተነሳስታችሁ 1984 የመሰረታችሁት ማህበር ነው ማህበሩ ከቁጥር በላይ የሆኑ እጅግ በርካታ ሥራዎችን ሠርቷል እየሠራም ይገኛል ይህ እውነት ነው ፡ ነገር ግን ይህ ማህበር ባሁን ሰዓት አርቆ ለሰው በቆፈረው ጉርጓድ ውስጥ እየገባ ያለ የሃያ አራት አመት ወጣት ማህበር ነው
የተከበርክ ወንድሜ ዲያቆን ዳንኤል ክብረት ማህበረ ቅዱሳን ከ 60 በላይ ባስ ሙሉ ሰው እየያዘ መንፈሳዊ ጉዞ እያዘጋጅ የአንዳንድ መምህራንን ስብከት እየቆረጠና እየቀጠለ በብዙ ሺ ኮፒ እያደለ ቅዱስ ሲኖዶስ ባልወሰነባቸው አገልጋዮች ላይ እነሱ ተሃድሶ ናቸው እያለ አገልጋዮቹን ከየቤተክርስቲያኑ እንደውሻ ሲያሳድዳቸው ድንጋይ ሲያስወረውርባቸው አንተ የትነበርክ ???
መዝሙርን ውስጡ ባለው መልዕክት ሳይሆን በዘማሪው ማንነት ወይም የማህበሩ ወዳጅ ነው አይደለም በሚል ብቻ እየተመዘነ በየግቢ ጉባዔው በየ ቦታው ሌብል ሲደረግ ምንም የማያውቀውን ምዕመን ፣ዘማርያን ፣አገልጋዮችን ግራ ሲያጋባ አንተ የት ነበርክ ???
ለመሆኑ ማህበረ ቅዱሳን ወደቤተክርስቲያን ባመጣው ሰው ልክ ባልባሌ ነገር ስንቱን ከቤተክርስቲያን ወደዛኛው አዳራሽ ገፍቶ ሲያስገባ አንተ የት ነበርክ
እሰቲ በማህበሩ አባላት የማያቋርጥ ወከባና ክስ ስማቸው የጠፋ ከቤተክርስቲያን የተሳደዱ ዛሬ የት ናቸው
አየህ ማህበረ ቅዱሳ የተዘጉ አብያተ ክርስቲያናትን ሲያስከፍት የስንቱን ልብ በአመጽ በጥላቻ በመለያየት እንደዘጋ አሁን ያለው ሁኔታ ምስክርነው ፡፡
በነዚህ ሁለት አስርተ ዓመታት ውስጥ ላባቶች የማይታዘዙ አባቶችን የሚንቁ ድንጋይ በየቤተክርስቲያኑ የሚወራወሩ ስለ ነጠላ አለባበስና ስለ ሌላው ግን የሚጨነቁ የሰንበት ተማሪዎችን በአንዳንድ ቤተክስቲያናት ያፈራው ከካህን መስቀል ይልቅ የፖሊስ መኖር ብቻ የሚያበርደው ወጣት ቤቤተክርስቲያኑ ያፈራው ይህ ማህበር አባቶችን መድፈር የተማረው ከናንተው መሆኑን በግልጽ እየታየ ነው
ወንድሜ ከዘነጋኸው ላታውስህ ማህበረ ቅዱሳን ማህበር እንጂ ሃይማኖት አይደለምኮ…..
ምነው እንደታላቅነትህ እንደመሥራችነትህ ልጆቹ አመጻን ሲሰብኩ መለያየትን ሲያውጁ አንዱን የአጵሎስ ሌላውን የጳውሎስ እያሉ ሲከፋፍሉ ጎንበስ ብለን ጉልበት ስመን ቀና ብለን መስቀል የሚያሳልሙንን አባቶች ሲያቃልሉ ባደባባይ ተዉ ለማለት አልደፈርክም ከቤተክርስቲያን የሳደዱዋቸው በዙ ክርስቲያኖች እምባ በቃላት እየጠለፉ ባደባባይ አንገት ያስደፏቸው ድንጋይ ያሰወረወሩባቸው ወንድሞች እንባስ አንዲሁ ይቀራል ……. የሁለት ሰዎችን የጥቅም ግጭት የሃይማኖት ግጭት አድርገው ባንድ ቤት ሁለት አይነት ምዕመን እንዲፈጠር ሲያደርጉ አንተ የት ነበርክ ….. ማህበሩ እኔ ያላጸደኩት መዝሙር ኦርቶዶክሳዊ አይደለም እኔ ይሁን ያላልኩት ሰባኪ ሰባኪ አይደለም የሚሉ እውቀት ሳይሆን እብሪት የተሞሉ ትምክህተኞችን ሰበስቦ ቤተክስቲያኒቱን ሲያምስ አንተ የታለህ ላንዳንድ የማህበሩ አባላት ቅዱስ ሲኖዶሱ መኖሩን የሚያምኑት እነሱን የሚደግፍ የሚመስል ውሳኔ ከወሰነ ብቻ እኮ ነው ካለዛ ማ ይኸው እንዲ በድፍረት ለመሳደብ የሚያግድ ጥቂት ስነምግባር ይጠፋል
እንደታላቅነትህ ይህንን ነገር መፍትሄ ታበጅለታለህ ብዬ እጠብቅህ ነበር
ደሞ ያንድን ማህበር ጉዳይ የሃይማኖት ጉዳይ አድርጎ እንዲህ ሀገርን ማመስ ተገቢ አይመስለኝም ለማህበሩ አሁን አይኑን ገልጦ ማሰቢያው ግዜ ይመስለኛል ምዕመኑ በቤተክርስቲያን ዙርያ እንጂ በማሕበር ዙርያ መሽከርከሩን እንዲያቆም መንገድ ማሳያው ፣ይሄንን አሳዳጅነት የፈሪሳዊ ሥራ ትቶ በአንድነት ስለቤተክርስቲያን እንደ ክርስቲያን እንዲኖር ማስተማርያው ጊዜ ላይ የደረሰ ይመስለኛል
የማህበሩ አባላት ሳውል ሆነው ያሳደዱትን አገልጋይ ምዕመን ስህተት ካለም በፍቅር ተራርሞ እንደ ቅዱስ ጳውሎስ ወደ ቤተክርስቲያን መመለሻው ጊዜ አሁን ነው
አንተም ወንድሜ ፖለቲካን ለብቻው ሃይማኖትህን ደግሞ ለብቻው ለይና ወደአእምሮህ ተመልሰህ እደግመዋለሁ ደአእምሮህ ተመልሰህ
ማህበሩ ለመልካም ነገር ይበልጥ እንዲተጋ ነገር ግን በማንኛውም መሥፈርት ከቤተክርስቲያን እንደማይበልጥ እንዲያውቀው ለማድረግ ትጋ ፡፡
ሁሉም ነገር እኮ ሥርዓት ና ደምብ አለው አባት ቢያጠፋ በቤተክስቲያናችን የሚመከርበት ሥርዓት አለው እኮ ቤተክርስቲያን ደሞ እንደካም አይነት ሳይሆን እንደያፌትና እንደሴም አይነት ልጆች ነው የሚያስፈልጓት
በድጋሚ የምነግርህ ማህበረ ቅዱሳን ማህበር እንጂ ሃማኖት አይደለም ፡፡
ደሞም አንተም ቅዱስ ፓትርያርኩን ከመሳደብህ በፊት ሃይመኖት የትርፍ ጊዜ ሥራቸው የሆኑትን ወጣቶች ብትመክራቸው የተሸለ ይሆን ነበር ነገ ቆሞ አውደ ምህረቱላይ ለመስበክ የማንን መስቀል ልትሳለም ነው ??? ሰይጣን ያልካቸውን ፓትርያርክ ወይስ ?????
በእርግጥ የጽሁፉ ርዕስ ከባድ ለሚስል ይችላል፡ ጉዳዩም ግን ከባድ ነው
Deleteኦርቶዶክስ ተዋህዶ ሀይማኖታችን መንገድ እንዲስት እይተደረገ ባለበት ወቅት፣ ሀገራችን በዘር በሃይማኖት ተከፋፍላ ልትፈነዳ በረደሰችበት በዚህ ወቅት ግራ የጋባቸው የሚመስሉ ወይም ያልገባቸው የቤተክህነት መሪ ጳጳስ ዝም እሚሉ ከሆነ ወይም ለሚሆነው ነገር ሁሉ መንገድ የሚያስተካከል ከሆነ፣ ይህ ጉዳይ ከልብህ ቆርቁሮህ ልትጽፍ ብትናሳ አንተ ብትሆን ምን ብለህ አርዕስት ትሰጠው ነበር፤ መዓዛ ሽታህ ታሀድሶ ተሀድሶ ቢመስልም እባክህ መልስልኝ
Iyoel Wendeme Endet newu ante kegrisawochu ena ketekmegnochu neh ende ? Betam yetekorekork meselk??? azagn mesay kibe Anguach endatehon tenkek Malet newu lemanegnawum Yimelesu yemetelachewu yeferetetu agelgayoch yalkachewu ene Aba onasen ene.... yemesaseluten kehone egziabher yegefawu eko egziabher yenekelewu eko esu balebetun tesetsito Yikerta kalteyeke Yalgefawu Mahibere kidusan limelesewu aychelem ena esti Tikmeh kekerebeh tikme kerebegn beleh begilts minale wey degmo Erdugn beleh teletone betazegaj yishalal . Dn daniel kibret yemisalemewu esacewun sayhon yanen yekerestosen meskel newu ??? eyeetenagere yalewu egziabher yesetachewun Siltane kehnet sayhon Yanen Ye patraryckenet kegziabher yetesetachewun siltan sayhon esun lemafres eyetega yalewun segawi aemerowachewun segawi astesasebachewun ena lebete chrestiyan yemeytekim manenetachewun newu lemanegnawum antem betehon keakalawiwu manenetachewu sayhon meskel yemetesalemewu egziabher kesetachewu siltane kehnet newu ena setesalem ke abune matiyas newu kalk tesastehal tilk mistir alewu kihnet tenkek belo memar memar mawek alyama fitsum nachewu ayatefum kalk aybelum aytetum aytegnum malet newu ayimekeru asteyayet ayisetachewu kalk kesewu zer aydelum letel newu selezih bizu newu tinitanewu wendeme rega rega rega malet tiru newu ewunetun ewunet malet egmo kefetari gar mesmamat newu wushetun adbesbeso ewunet newu eyalu siyatefu mesmamat gin mot newu.
Deleteቃለ ህይወት ያሰማልን ወንድምአለም
Deleteአገላለፅህ ጠንካራ ቢሆንም እውነቱ ግን እንደፃፍከው ስለመሆኑ የአደባባይ ምስጢር ነው፡፡ስለሁሉም መገፋታችን ዝምታን መምረጣችን ተገቢ አይመስለኝም፡፡የማኅበሩ አመራርም አስፈላጊውን መስፈርት ሁሉ አሟልቶ አውደ-ርዕዩን ለማቅረብ ፈቃድ አግኝቶ ከማዕከሉ ጋር ውል ከገባ በኋላ በአስራ አንደኛው ሰዓት መከልከሉን በዝምታ ማለፍ የለበትም፡፡ማኅበሩ ህጋዊ መንገዶችን ሁሉ ተከትሎ ተሰጥቶት ”የተነጠቀውን” መብቱን ማስከበር አለበት፡፡ጉዳዩንም ወደ ፍ/ቤት መውሰድ እንዳለበት ይሰማኛል፡፡
ReplyDeleteዲ/ን ዳንኤል እግዚአብሔር ብእርህን ያበርታ። ቃለህይወት ያሰማህ።
ReplyDeleteእኔ ግን የምለው፣ የፓትርያርክነት በትረ ስልጣኑን ዲያብሎስ ይዞት እያስተዳደረ ሳይሆን አይቀርምና እንጸልይ፣ የቤተክርስቲያን ፓትርያርኳ እስኪገኝ ድረስ።
እግዚአብሔር ይስጥልን
ReplyDeleteባወቅሁት እና በተረዳሁት ነገር ጳጳስ የሚሾመው ያለው ሲሞት(ሲያልፍ) መሆኑን ነበር እና ለምንድነው አሁን የማይሾመው??
ReplyDeleteÃH@ ÓTi T>K=Ä” w` ²^ò }wKA ¾}ÑKì¬ የማነ ዘመንፈስ ቅዱስ የሚባል ጋዜጠኛ ወ ሊቀ ማእምራን እንዴት ያለ ክብረ ቢስ ነዉ፡፡ እንዴት በተዘረፈ ብር ልጅን የሚያህል የአምላክ ስጦታ ያሳክማል፡፡ ልጆች እኮ የእግዚአብሔር ስጦታዎች ናቸዉ፡፡ እኔ ለልጁ ምጥፎ አልመኝም ታሞ ከሆነ፡፡ እሱ ግን ክአምላክ ቁጣ የሚያመልጥ አይመስለኝም ንስሃ ካልገባ፡፡
ReplyDeleteedehulgizew ywstachenn geltsehlnal lezihm tegdaroteh egzabher yistln blenal
ReplyDelete"danye kidame maletim 17-07-2008 kidus ouraeal lay yetederegew neger hizibe kirsitianu belelet tesebisibo bememihir girma lemetemek yekidase sinesiriat endaleke endayatemiku kepatireyarku debidabe tenebeb bezeyangeze hizibu kekifile ager sayiker yemeta ale enam hizibu bilom tamamewoch kebetekirstian yalekesut emiba temaro bewunet egizeabher anid neger kalassayen bilo malikes yehizibe emiba manew halafenetun yemewosid daneye yih yekirstean emiba legers tiru new endet ayehew bantebekuls milash beset kante des yilenal yetegodaw hib
አመሰግናለሁ፥ዳ/ን ዳነኤል የኛ ችግር ብዙ ጊዜ ጠማማን ጠማማ ማለት አንደፍርም ፥ እየሆነ ያለው ግን ስትናገር በርግጎ የሚያስበረግግ ልወደደ ባይ ትውልድ በዝቶ ስትገስፅ ወይም የሚበጀውን ስትናገር ከአመፀኛ ጎራ ይፈርጃሀል ፥ ያም ይሁን ይህ በዘመናችን በአለም ስንከፋ የምንጽናናባትን አንድ መጠጊያ የሆነች ክርስቶስ በደሙ የዋጃት ቤተክርስትያንን የሚጠብቅ ትጉህ እረኛ የለንም።ለዚህ ነው አንዳንድ ወንድሞች የኢኦተቤተከርስትያንን በመተው ወደ ግሪኩ ወደ ግብጹ የሚኖጉዱት መቼ ይሆን የኛ የምንለው እረኛ የምናናኘው እርግጥ ሰው ይስታል ግን በጎቹን ግን ወደ ገደል አይጥልም።አንተ ግን ምክር አዘል ተግሳጽህን ቀጥል።
ReplyDeleteአምላከ ቅዱሳን ልዑል እግዚአብሔር እንዲህ ለሀገርና ለሃይማኖት ዘብ የሚቆሙ ምእመናንን አያሳጣን። ዲ/ን ዳንኤል ክብረት ልዑል እግዚአብሔር በእድሜና በጤና በሃይማኖትና በምግባር በሀብትና በፀጋ ይጠብቅ። የአገልግሎት ዘመንህን ይባርክልህ።
ReplyDeleteWhat is the purpose of this message? Daniel your comments can make a difference if you presented in a positive I am ok with critic's but the way you did it is wrong because MK is responsible for the disruption of our Church. I agree problems on both side but as it has been done before why MK don't want to listen and follow tell church leaders advice so they put positive dent in our beliefs. In my view b/c of financial strength MK have it or number of members, might think or thinking to split the church or involves in politics as it seems from your comments or from what it has been observed.
ReplyDeleteWe have special recognition for you as our teacher of the gospel but Some times you makes us confused how to define you, why don't you confront the church leaders and challeng them and make a difference instead of ye stihuf Wigya.please make a positive difference
ዲያቆን ዳንኤል እግዚያብሔር አገልግሎትህን ይባርከው፡፡
ReplyDeleteለአቡነ ማትያስም እግዚያብሔር ወደ ልቦናቸዉ ይመልሳቸው
ሁላችንም ፆሙን በርትተን ፈጣሪያችን እንጠይቀው ምላሹን በጥቂት ቀን ያሳየናል፡፡
aye aba Matias Lezche Edme Corider laye lekomebat mognet new andande yigermgale lengru tenbitu yiftsem zend ged new.
ReplyDeleteDiakon Daniel Egzuabher Anten ayastan kerwe gezhen yibarkew
This contradict everything what you advocated in the past our church issues. This article is has a lot of good substances and reality. However, your disposition before was just to stay clam and accept what ever the church leaders said. You was one of the people who advocated to break the link between the two church groups ..(The America and The Ethiopia). We all knew the Ethiopia one was been corrupted and a fake one, but because of your and other people agendas we missed the time to fix our church.
ReplyDeleteGood article but tool late!
ዳኒ የተናቀችውን የደቡብ አፍሪካዋን ቤተክርስቲያናችንን መገፋት ስላነሳህ እግዚአብሄር ይስጥልን ለአጠቃላዩ ምእመናን እንዲያውቁት እውነትም ተዳፍኖ እንዳይቀር ይህንን ለመላው ዓለም አድርስልኝ አቦ ገብሬል ይባርክህ ዋናውን ጉዳይ ነቄ ብለኽዋልና ይቺን ለኦርቶዶክሳዊዎች ሁሉ አድርስልኝ ቅፈላ መሮናል ቤ/ክ ሲሆን ደግሞ ይደብራል አይመችም
ReplyDelete1_ከለታት በአንደኛው ቀን በደቡብ አፍሪካ ችግር ተፈጠረ
2_ሊቀጳጳሱ እና የ ፕሪቶሪያ ኪዳነምህረቱ መነኩሴ በሲኖዶስ ውሳኔ ተነሱ
3_ሥራ አስኪያጅ የተባሉ ተልከው በቪዚተር ቪዛ መጡ
4_ሕጋዊ የሥራ ፈቃድ አልነበራቸውምና ከሰበካ ጉባኤ ጋር ስላልተግባቡ ተመለሱ ተባለ
5_ቆየት በአሉና በረዳት ሊቀጳጳስ ማእረግ ተመልሰው መጡ ቀጣሪያቸውም ከፕሪቶሪያ የተባረሩት መነኩሴ ነበሩ ለራሳቸው ተባርረው ሕጋዊ ሳይሆኑ ለሥራ ፈቃድ ፈረሙላቸው ይላሉ ፡ ሕዝቡ ነቄ አለ መነኩሴ ሲሸውድ ሸውዶም ሲነቃበት አይመችምና
6_ሕዝቡ እንዲህ የሚባል ሥልጣን የለም ብሎ ፈተለባቸው
7_ሽማግሌ አታሪዎች ሰርተው ለሲኖዶስ አቀረቡ
8_በሲኖዶሳችንም ሁለት ጳጳስ አንድ መነኩሴ አጣሪ ተብለው ተላኩ መነኩሴው በነገራችን ላይ በአዲሳባው ሲኖዶስ መናፍቅ ተብሎ ተባርሮ የነበረ እና አሜሪካ ገብቶ ቆቡን ጥሎ ታክሲ ነጂ ሆኖ ከርሞ እዚያኛው ሲኖዶስ ወጣ ገባ ሲል ቆይቶ ፋዘር አስመጥተው ዋናው ቤተክህነት የውጭ ግንኙነት መምሪያ ፈላጭ ቆራጭ አድርገው ያስቀመጡት አጭቤ ነው ጊዜ ይፈታዋል ወይም እነ አቡነ ማርቆስ በቅኔ ይፈቱታል
9_ ሥራአስኪያጁ ከጆበርግ ጨሴዎች ጋር አጣሪዎቹን አፋዝዘው የእንቅልፍ ፒል ሊያዘጋጁ ወሰኑ በቀጥታ በአቡነ ሉቃስና በንቡረ እዱ በኩል ለዋናው ፋዘር እና ለቋሚ ሲኖዶስ አባላት የሚወጋ አሪፍ ነገር፡ እኛ ታውን ሲወራ ውሸት ይመስለን ነበረ አሁን ሳስበው ግን ለክ የነበረ ይመስለኛል
10_ በመሀል ከሁለቱ ጳጳሳት አንዱ ነቄ አሉና በሕዝብ ፊት ጉዳዩን አፈረጡት በተፈጠረውም ጉዳይ አዝነው ለብቻቸው ቀድመው ተመለሱ ተባለ
11_ 1ዱ ጳጳስና ታሪከኛው የኦክላንድ መነኩሴ አንደር ግራውንድ ለቅዱስ ሲኖዶሱ አባላት የሚደርስ ፈንድ ሬዝ ሲያደርጉ ከአጋቹ ቡድን ጋር ሲሞዳሞዱ ቆይተው "በአስቸኳይ መልስ ይሰጥበታል" ብለው ቀፍለው ተመለሱ ፒፕሉም እነዚ ከሲኖዶስ የመጡ ናቸው ወይስ ከታውን የመጡ አስዘላዮች ብሎ ተገርሞ ከረመ
12_ ሕዝቡም ሰፍ ብሎ ፡ ሀይማኖቴን የሚጠብቅ ሲኖዶስ፡ ለእውነት የቆሙ አባቶች ይህን ያርሙልኛል ብሎ ሲፋዘዝ ዳኒዬ አንተም ነቄ አልክ "እንዳልከው ዋናውን ሰውዬ እና በዙርያቸው ያሉትን የእንቅልፉን መርፌ ወጓቸው እናም አንተም ነቄ እንዳልከው ፋዘር አንቀላፉ ሲለዚህ ክህነት እና ምንኩስና ሲኖዶስና የአባቶች ታማኝነት ዜሮ ገባ አገር ያወቀው ጠሀይ የሞቀው ሌብነት ለመሸፈን ሲሞከር ዜኖፎቢያ ያቃጠለው ሳያንስ አባቶቻችን በሙስና ተሸብበው መንፈሳዊነታችንን አዋረዱት " እንደተባለው በስማበለው ሲዋጣ የነበረው ገንዘብ በእቅልፍ ፒል ስታይል ለፋዘርም ለፋዘሮቻችንም እንዳልከው ድሆ ድሆ ደረሰ ማለት ነው
እግዚአብሔር ይጠብቅህ ከተጨማሪ የታውን አፕዴት ጋር እመለሳለሁ
Great!
ReplyDeleteIt is a correct comment and timely. It is not late to correct the problem if the Patriarch has a humble interest for the sake of the church.
ReplyDeleteአንተ የሚሊኒየም ጀግና በቃ ምን ልበልህ .....የ አንተ ጽሁፍ በብዙወቻችን ህይወት ውስጥ አለ: ፍሬ አፍርቷል።አስተያት ሰጭወች ግን ይገርሙኛል፣በቤተክርስቲያን ታሪክ አትናቴወስ በነበረ ጊዜ እርዮስ ነበረ፣በጳጳስ ተብሎ ሙስሊም መጥቶልን ነበረ፣ዛሬም እነ ኪነጥበብ በዘመሩበት እነ ዘርፌ እየዘፈኑበት ፤እነ ቀሲስ ደጀኔ በሰበኩበት እነ አሰግድ እነ በጋሻው እየጮሁበት እያየን: በነ እቡነ ተክለ ሀይማኖት መንበር ካድሬ መቀመጡን እንዴት ልባችን አላስተውል እለ?
ReplyDeleteመምህር ዳንኤል ይች የማህበረ ቅዱሳን አመራርን(በአሁኑም እግዚዓብሔርስ ምን አለ በሚለው ፅሁፍም,...በሌላም) ነካ ምታደርጋት ነገር በጣም ተገቢ ነች።አንተን እሟሟሟ....
ለውድ መምህራችን ዲ/ን ዳኒኤል ክብረት
ReplyDeleteየከበረ ሰላምታዬ ይድረስህ፣ እግዚአብሔር እድሜና ጤና እንዲሰጥህ ዘወትር እለምናለሁ፡፡
ማኅበረ ቅዱሳን የቤተ ክርስቲያንን ሥራ በቅንነትና በታማኝነት ባይሠራ ኖሮ ልንወደውም ሆነ ገንዘባችንን፣ ጊዜያችንን፣ እውቀታችንን እና ጉልበታችንን በደስታ ለመስጠት ባልቻልንም ነበር፡፡ ውድ ዲ/ን ዳኒኤል፤ እስኪ ማኅበርን ከቤተ ክርስቲያን ለማስተካከል ትሞክራለህ ለሚሉህ ልበ ስውራን ባለፉት 23 ዓመታት ቤተ ክህነቱ በስብከተወንጌል፣ በገዳማት፣ በአብነት ት/ቤቶች ወዘተ የሠሩትን ና ማኅበረ ቅዱሳን የሠራውን የሚያነጻጽር መረጃ በነካ እጅህ አቅርብላቸው፡፡ መረጃው ጥያቄውን ከሚያቀርቡት የተሰወረ እንደማይሆን አውቃለሁ፡፡ በንጽጽር መቅረቡ ግን ለእነርሱ ባይጠቅማቸውም እነርሱ የሚያንሸዋርሩት የዋሁ ምእመን እውነታውን ማየትና መገንዘብ ይችላል ብዬ አምናለሁ፡፡ እንዲህ አይነት ጥያቄ ለሚያቀርቡና በልባቸውም ለሚያመነቱት ግን አንድ ጥያቄ ላቅርብ፣ ቤተ ክርስቲያንና ማኅበር የተለያዩ የሚሆኑት መቼ ነው? ማኅበሩ የቤተ ክርስቲያንን ሥራ ካልሠራ ብቻ አይደለምን? የቤተ ክርስቲያንን ሥራ ከሠራ እንዴት ይለያያሉ? የአንዱ ጥቃት የሌላው የማይሆነው እንዴት ነው? ይህንን ከልበ ስውራን በቀር መገንዘብ የሚከብደው ማንም የለም ብዬ አምናለሁ፡፡ ልበ ስውራንን ይማርልን፤ አሜን፡፡
አምላከ ገብረ መንፈስ ቅዱስ ይስጥልኝ
Deleteበአብነት እና በመንፈሳዊ ኮሌጅ ባታልፍም ከረጅም ዓመት ንባብ እና ከእድሜ የተማርክ ትመስለኝ ነበር፡፡ለካ በጭብጨባና በደጋፊ ብዛት ታውረህ በዚሁ መስመር ቁልቁል የምትራመድ ሰው ነህ፡፡ምን ከምን ተነጻጽሮ እንደሚጣፍ እንኳ ሳታውቅ ስሜታዊነትን እንደቀናኢነት ቆጥረው በስሜጥ ሽምጥ የሚጋልቡ የማኅበረ ቅዱሳን አባላትን ጭብጨባ ለማግኘትና ለመጽሐፍህ ገበያ አብዛኛው ተደራሲ የሚገኝበትን ስሌት በመስራት የጻፍከው ነውረኛ መጣጥፍ ለራስህ አለማሳፈሩ ያስገርማል፡፡ ቅሬታን ለማቅረብ ስንት የለዘበ መንግድ እያለ እንዲህ አይነት ልቅ ርእስ በአንዲት የቤተክርስቲያን ርእሰ መንበር ላይ መጠቀም እድሜና ንባብ ያልለወጠህና በጭብጨባ ያበድክ ተራ አማተር መሆንህን ከማስመከስከር ውጭ ጠቀሜታ የለውም፡፡ የማዝነው አንተን እንደአርአያ ተከትለው በየፌስቡኩ፣ብሎጉ እና የግል ጋዜጣው አባትን ማራከስ እንደትልቅ ሞያ ለተያያዙት ውሪዎች ነው፡፡እናንተማ አንድ ጊዜ ተጣማችሁ ነውራችሁን የአባቶች ድክመትና የቤተክህነት መዝረክረክ የሚደብቅላችሁ መስሎአችሁ ጎዳናውን ተያይዛችሁ ወደ እርግና ተጠግታችኋል፡፡
ReplyDeleteበእርግጠኝነት የምነግርህ ማንኛውም በአባቶች እግር ስር ያደገ ደቀመዝሙር ይህን መደዴ ጽሑፍህን አያደንቅልህም፡፡እንኳንስ ከታች ወደላይ ከላይ ወደታች እንኳ አባቶች ልጆቻቸውን ሲገስጹ ወግ አለው፡፡እንዲህ አይነት ገና ከርእሱ ጀምሮ በስድብና በማንጓጠጥ የተሞላ ጽሑፍ ከትበህ የተሳዳቢዎች ቁንጮ ለመሰኘትና በወቅታዊ አለመግባባት ስሜታዊነት ውስጥ የገባውን የማኅበር አባል ትኩረት ለመሳብ ያደረከው ርካሽ ጽሑፍ ርካሽ ተወዳጅነት ለማግኘት ከማሰብ የመነጨ ነው ከማለት ውጭ ሌላ ትረጉም የለውም፡፡ራስህን ለጭብጨባ አስገዝተህ ለቤተክርስቲያን የነቀፋ አብነት ከመሆን በጊዜ ጥሩ የግል ጋዜጣ ወይም መጽሔት አቋቁመህ ሚናህን ለይ፡፡በዚህ መጣጥፍ መጥላት ብቻ ሳይሆን ንቄሀለሁ፡፡ሁለተኛ ወደብሎግህ አልመጣም፤ላይህም አልፈልግም፡፡እስካሁን አንተን እንደጥሩ መምህር መከተሌም ይቆጨኛል፡፡ራሱን ለርካሽ ጭብጨባና ዝና ሚያስገዛ ሰው ስለማልወድ አንተ ላይ ልደብቀው የማልችል ጥላቻ አድሮብኛል፡፡
ወንድሜ.
ReplyDeleteበዚህ መጣጥፍህ ከርዕሱ እስከ መደምደሚያው በቅዱስ ፓትርያርኩ ላይ ስላዘንብከው አጉራ ዘለል የቃላት በረዶ አሁን ሰፊ አስተያየት አልሰጥም። አንድ ጥያቄ ግን ልጠይቅህ።
አውደ ርርርዩን የኤግዚቢሽን ማዕከሉ እንዳገደው በይፋ ነተግሯል።፡ታዲያ ይህንን እገዳ ፓትርያርኩ እንዳደረጉት ደምድመህ የጻፍከው ከምን ተነስተህ ነው? የጸሐፊስ ወጉ ይህ ነውን? “... መጽሐፉ እንደሚል ‹የማይገለጥ የተሠወረ› አይኖርምና ዐውቀነዋልም፣ እናውቀዋለንም፡፡” ብለሃል። እንዴት አወቅህ? በጥንቁልና?! በነገራችን ላይ ስለጠንቋይ ብዕርም በዚሁ ጽሑፍህ ስላነሳህ አባትህን ክፉኛ አስታወስከኝ።
I thank God, who I've you the power to speak the truth. God bless DeAR Btother.
ReplyDeleteመልካም ምላስ ቁጣን ታበርዳለች የዳንኤል ጩኸት ግን ማስተዋልና መታዘዝ ታፈርሳለች᎓᎓ ዳንኤል ሆይ! የኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተክርስቲያን ፓትርያርክ በመንፈስ ቅዱስ እንደሚመረጥ እናምናለን᎓᎓ ሲኖዶስም ዲድስቅልያም ይናገራሉ᎓᎓ ለምንድነው ፓትርያርኩ የምትዝልፍ? ስለማይከሱህ? ስለማያስፈራሩ? የጸሎት አባት ስለሆኑ? በቤተክርስቲያን ተጠግተው የሚዘርፉትን አገልጋዮችም ማህበራትም በግልፅ በመግለጫ ስለተቃወሙ? ዳንኤል ስለምን ትዘልፋቸዋለህ? ለእድሜህ ለመሰረትከው ቤተሰብ ጥሩ ይሆናል? ደግሞስ እንዲህ ያለ አባባል የፖለቲከኞች እንጂ የኦርቶዶክስ ተዋህዶ እምነት ተከታይ የሃይማኖት ሰው ነኝ የሚል ቋንቋ ነው? ዳንኤል የኢትዮጵያ መንግስት እንዳንተ ባሉ ባለ አስር ምላስ ብእር ይደናገራል ወይም ይደነግጣል ብለህ የምታስብ ከሆነ የዚህ መንግስት መሰረት ለማወቅ ብትሞክር ይሻልሃል᎓᎓ እንደ ኦርቶዶክሳዊ ወግና ስርአት ሃሳብህ ብትገልፅ መልካም ነበር ነገር ግን ፓትርያርክን ያክል አንተ እያልክ ስድ የሆኑ ቃላት እየተጠቀምክ ለማስፈራራትና ለማሳመፅ ያደረግከው ሙከራ መልካም አልመሰለኝም᎓᎓ የመናፍቅነት መጀመሪያ ቀኖናን መጣስ መጀመር ወይም እንዲጣስ በፅሁፍም በቃልም መስበክ ነው᎓᎓ ዳንኤል ፓትርያርክ መዝለፍ ለፓትርያርክ አለመታዘዝ የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ሃይማኖት ስርአት አይደለም᎓᎓ እስከማውቀው ያስወግዛል በምድራዊ ስርአትም ያስጠይቃል᎓᎓
ReplyDeleteEyouel, ምናልባት መንገድ የጠፋበት ሰው ትመስለኛለህ። የሙስናው ተካፋይም ሳትሆን አትቀርም ። ማህበሩንና ዳንኤልን ለቀቅ የገንዘብ ምንጭህን ጠበቅ።
ReplyDeleteቃለ ህይወት ያሰማልን፣ ጸጋውን ያብዛልን!
ReplyDeleteiyouel solomon??? ሰይጣን ያልካቸውን ፓትርያርክ ወይስ ?????
ReplyDeleteበንጽጽር የማሰተማር ዘዴ የአባትንና የሰይጣንን ግብር ገለጠ እንጂ አልተሳደበም፡፡ቋንቋ ብትማር መልካም ነው በተለይ figures of speech like metaphor,simile,hyperbole etc ይልቁንም ከሀሜት ያለውን ነገር በጥበብ ማሳሰብ ስድብ አይሆንም የፓትርያሪኩን አማካሪዎች ልብ ይስጥልን፡፡አንተም ልብ ይስጥህ፡፡ጌታ የማይፈርድ እንዳይመስልህ፡፡
የመናፍቃኑ ብሎጎች ፣ መጽሔቶችና ጋዜጦች በአንድ ድምጽ ይህ "ጸረ ክርስቶስ " የሆነ ማኅበር የሆነ ማኅበረ ቅዱሳን የተባለ ደንቃራና " ገገማ " ማኅበር ካልፈረሰ ደስ አይለንም እናም አሁን የተጀመረው ሁኔታ ተጠናክሮ ይቀጥል ማለታቸውና ድምጻቸውን ከፍ አድርገው " ብራቮ " አቡነ ማትያስ ማለታቸውን ባየሁ ጊዜ ልቤ ጠረጠረና ማኅበሩን ይበልጥ ወደድኩት ።
ReplyDeleteቤተክርስቲያኗ ግን ለውለታዋ ይከፈላት ይገባ የነበረው ይህ አልነበረም። ለኢትዮጵያ ከቡናና ሌጦ በላይ የውጭ ምንዛሪ ያለገደብ የምታስገባ ናት ። የመስቀል ፣ የጥምቀት ፣ የዓደባባይ በዓላቶቿን ለማየት ፣ አክሱም ላሊበላ ፣ ጎንደር ዋልድባን ፣ ደብረዳሞ ዝቋላን ፣ ቁልቢ ግሸንን ፣ ደብረሊባኖስ ዙር አምባን ለማየት የሚመጣው የውጭ ሀገር ሰው ለሀገር የገቢ ምንጭ መሆኑ እሙን ነው ። እናም ይህችን ቤተክርስቲያን ገለል ፣ ገሸሽም ማድረግ መበርከቱ በግሌ አስግቶኛል ።
በማእከሉ ፕሮቴስታንቶች ያለ ከልካይ ዝግጅታቸውን ያቀርባሉ ። የንግድ ድርጅቶችም እንዲሁ ። ከአውሮፓና ከአፍሪካ ሀገራት የመጡ የንግድ ሰዎች ይጠቀሙበታል ። ለዘፈን ኮንሰርት የሃይማኖት ድርጅቶችም ዝግጅት ይካሄዱበታል ። ታዲያ ለኦርቶዶክስ ሲሆን ምነው ምነው ወገቤን ተባለ?
ያየኸውን እና የሰማሁን እንድታቋድስን የሰላ ብር ለሠጠህ ለልኡል እግዚያብሄር ምስጋና ይግባው ጭቃን ጭቃ ነው የሚል ትውልድ በጠፋበት ዘመን አንድ ብለህ መጀመርህ ከልቤ አመሰግንሃለሁ ያየኸውን እና የሰማሁን እንድታቋድስን የሰላ ብር ለሠጠህ ለልኡል እግዚያብሄር ምስጋና ይግባው ጭቃን ጭቃ ነው የሚል ትውልድ በጠፋበት ዘመን አንድ ብለህ መጀመርህ ከልቤ አመሰግንሃለሁ
ReplyDelete"የዕውቀት ጣራ ላይ መድረስ አንጋጦ መዝለፍ ነው!" ብለህ ከዚህ ቀደም ስለ አቡነ ጳውሎስ በፃፍከው ጽሑፍህ አስነብበኸን ነበር ዲ/ን ዳንኤል ክብረት ዳኛ እና የምርጫ ቦርድ አስፈፃሚ እንዲሁም ሸምጋይ ገለልተኛ /Neural /አካል ካልሆነ ፍርዱ ቀና አይሆንም በርግጥ የውስጥ ችግሮች ሊኖር ይችላል ነገር ግን ሁሉንም ተግዳሮቶች በጠረጴዛ ዙሪያ መፍታት እየተቻለ የቤ/ክ ምስጢር አውጥቶ ለማይመለከታቸው ምዕመናን መዘርገፍ ሆድ ለባሰው ማጭድ ከመሆኑም ባሻገር ምዕመናኑ ለቤ/ክ አባቶች ንቀት እንዲያድርባቸው የሚያደርግ ስለሆነ ጽሁፍህ እርማት የሚያስፈልገው ነው ባይ ነኝ በሌላ በኩል ከላይ 1 አስተያየት ሰጪ የሰነዘረውን አስተያየት ተመልክቼው ነበር በርግጥም "ስውሩ አመራር" ብለህ ያስነበብከን ፅሑፍ አንተ በአንድ ወቅት ከማህበሩ ጋር በነበረህ መሻከር በስሜታዊነት ይሁን በስማዊነት የፃፍከው ፅሑፍ አንደሆነና እርሱም ቢሆን ከፀብአጫሪነት የዘለለ ቁም ነገር አዘል ትምህርት እንደሌለው እኔ በበኩሌ አልጠራጠርም ምክንያቱም በጊዜው አንተ ለማህበሩ የሰጠኸው አጸፋዊ ምላሽ ቢሆንም ያንተንና የማህበሩን አለመስማማት ምዕመኑ ማወቁ ምን ፋይዳ አለው? ለማንኛውም ዲ/ን ዳኒ ብዙ ቢያወጉ ይዘነጉ፡ ብዙ ቢተቹ ይሰለቹ ነውና ብሂሉ እንደዚህ አይነት ህዝቡን ከ አባቶች የሚያጋጭ ነገር የአደባባይ አዋጅ ከማድረግ ይልቅ በችግሩ ዙሪያ ከሚመለከታቸው አካላት ጋር በውስጥ ጉባዔ በመፍታት ለምዕመናኑ ብስራትን መንገር ተገቢ ነው ባይ ነኝ እግዚአብሔር ኢትዮጵያን ይባርክ!!
ReplyDeletethanks D. Dani. it express every thing 101% true.
ReplyDeleteJelewochu enkuan yanten tsihuf likebelu, Geta beakal bimeta ayikebelutem.
ReplyDeleteአጨብጫቢዎች ሆይ ቤተ ክርስቲያንን ብቻ ሳይሆን ሰውየውንም አወዳደቁን ታላቅ እያረጋችሁበት ነውና ወደልቦናችሁ ተመለሱ።
ReplyDeleteምከራችሁን ለለገሳችሁለት ግን በቲፎዞ ጭሆት የሰከረን በቀላሉ መመለስ ከባድ ቢሆንም አክብሮቴን ልግለጽላችሁ። አምላክ ሆይ ከዘመነ እንስሳነት ወደ ዘመነ ለብዎ መልሰህ ሰላምህን ስጠን። አሜን
የቀሲስ ዳንኤል ክብረትን ጽሁፍ አንብቤአለሁ አልታነጽኩበትም እንጂ።
ReplyDeleteክርስቲያኖች በመከራቸው ጊዜ ሲጨነቁ (ሲጨመቁ) የሚወጣቸው ምን እንደሚሆን ጌታችን ሲያስተምረን “የሚሰሩትን አያውቁምና ይቅር በላቸው” የሚል ቃል በመስቀል ስብከቱ ተናግሮአል። ዛሬም ይህ የጌታችን ጸሎት ይሰራል እስከ አለም ፍጻሜም ሲሰራ ይኖራል። ከጌታችን የተማሩ እውነተኞቹ ክርስቲያኖች እንደነ ቅዱስ እስጢፋኖስ ያሉ ቅዱሳን ሰማዕታት ይህን የከበረ ቃል ደግመው ተናግረዋል። አብዛኞቹ ቅዱሳን በመከራ ሲያልፉ ከድግስ ቤት ጠግቦ እንደሚወጣ እድምተኛ ደስ እያላቸው በጌታቸው ሐሴትን እያደረጉ በስድብ በግርፋት በንቀትና በውርደታቸው ስለስሙም በመገፋታቸው ከአምላካቸው የክብር አክሊል እየተቀዳጁ በፀጋ ላይ ፀጋ ሲጨመርላቸው አይተናል ሰምተናል አንብበናል። ታዲያ የቅዱሳን ልጆች ነን ብለው ከቅዱሳን በረከትን ለማግኘት ማህበራቸውን “ማህበረ ቅዱሳን” ብለው ሰይመው የቅዱሳን ልጆች ተብለው እራሳቸውን ጠርተው እንዴት በቅዱሳን ግብር መገለጥ አቃታቸው። የዝግጅቱ አለመቅረብ ለማህበሩ አባላት ከባድ ፈተና ሆኖ ሊሆን ይችል ይሆናል። ይሁንና ሁሉንም ለበጎ ነው ብሎ ለመቀበል መቸገር አልነበራቸውም። ከመስዋዕት መታዘዝ ይበልጣልና በእሽታ ቢያልፉት ታላቅነታቸው ይገለጥ ነበር። ነገር ግን እግዚአብሔር ሁሉን ለበጎ ያደርጋልና ማንነታቸው እንዲገለጥ ይህን ፈተና አመጣ ማኔ ቴቄል ፋሬስ ሆነ። የሚሰዱባችሁን መርቁ ለሚያሳድዱአችሁ ጸልዩ የሚለውን የእግዚአብሔር ቃል በመተላለፍ በቤተክርስቲያኗ ከፍተኛ ስልጣን ላይ የስድብ ናዳ አወረዳችሁ። የተሰደቡት እሳቸው ሳይሆኑ በብዙ ሚሊዮን የምንቆጠረው የቤተክርስቲያኗ ልጆች ነን። እግዚአብሔር በቤቱ የሾመውን በጊዜው ለማንሳት ብቃት እንዳለው እናምናለን። ይሁንና እኛን ባልተመቸን ቁጥር ግን እግዚአብሔር በቀባው ላይ እጃችንን ለማንሳት አፋችንን ለማላቀቅ ብዕራችንን ለመሳል ድፍረት የለንም (ካመናችሁ ያለእግዚአብሔር ፈቃድ ምንም እንደማይሆን)። በእርግጥም የከለከሉት እሳቸው ቢሆኑስ በልጅነት መንፈስ መጀመሪያ በመጸለይ ተግሣጽም ቢኖር በአግባቡ ማድረግ ሲገባ እንዲህ ያለ አሳዛኝ ጽሁም በአለም መበተን እጅግ ያሳዝናል። መቼም ቀሲስ ዳንኤልና ማህበረ ቅዱሳን ያንድ ሳንቲም ሁለት ገጽታዎች እንደሆኑ ይታወቃል። የማህበሩም አቋም ይህ ከሆነ ቤተ ክርስቲያን ያለችበት ሁኔታ እጅግ ያሳዝናል እርስ በርስዋ የምትለያይ መንግስት ቤትም ቢሆን አይጸናም ብሎናልና ጌታችን። ስለዚህ ቤተክርስትያን እጅግ ልታስብበት ይገባል። ቢያንስ በአለም የስራ ስፍራችን ያሉትን አለቆች የምናከብረውን ያህል ክብርና መታዘዘ እንኳን ለቤተክርስቲያን አባቶች ልናሳይ ይገባል። ዛፍ በፍሬዋ ትታወቃለችና ቀሲስ ዳንኤል ያሳዩት ፍሬ መራርና መርዝ የሞላበት ነውና ብዙዎች በልተው እንዳይታመሙ ቀሲስም ለመረገም እንዳይቀርቡ ከወዲሁ ለይቅርታ ብዕራቸውን አንስተው የበደሏትን የሰደቡአትን ቤተክርስቲያን (ማህበረ ምዕመናንን) ይቅርታ እንዲጠይቁ በትህትና እንጠይቃለን። ከማህበረ ምዕመናን ለመለየት ዳር ዳር እያለ ያለውን ማህበራቸውን ወደ ማህበረ ምዕመናን እንዲያስገቡ (ከታሪክ ተወቃሽነት) እንዲተርፉ እናሳስባለን። የቤተ ክርስቲያን ራስ ክርስቶስ ልብና ልቡናን እንዲሰጥዎትም እንጸልያለን።
Erew wwendeme wey ehte yihenen asteyayet lemestet medkem metsaf ayasfelegehm ke Addis Ababa adbarat astedadariwoch gar bemehon akuamehin betgelts ena ezawu yeakuam meglecha ley bikateteleh gizem genzebem gulbetem awuteteh metsfeh kisara honebeh aymeslehem????
DeleteTo all the Anonymous commentators above: 1st, it is Dn Daniel, not qesis Daniel.
Delete2nd, the church fathers are not beyond fault. Otherwise we wouldn't be in this mess right now. So, somebody has to stand up for the truth.
3rd, don't be a chicken shit and hide behind anonymous comments. Give your name if you dare.
Please always think deep before you start your bla bla bla... boring
Think of the church 1st.
Hope that gives you something to think about.
Dear Anonymous March 31...
DeleteYou said የቀሲስ ዳንኤል ክብረትን ጽሁፍ አንብቤአለሁ አልታነጽኩበትም እንጂ።
1. The first thing where do you get Kesis
2. Building oneself mainly is dependant on the person himself, especially like you. Because you have reached in a subconsciousness of understanding a written piece.
From your comment I understand that for your spiritual maturity Daniel has his own input. If so you better question your self... is my understanding because of my level... Do I know the status of my church... What makes him to do the one that I believe should not be done... Is that because of his maturity or stupidity...
3. When do we obey to our Pope, and to how much extent should we tolerate our Pope?. Should our tolerance extend till our church characteristics gone wild. When is the time to say this is not our forefathers Pope's behavior.I think it is very clear for all us that we are not Monks to tackle things only via prayer.
4. Why you give a tag to his Piece of writing. It is Daniel's view, if MK shares well it is interesting, but there is no any evidence to say that. And what you should have to know is MK is for our precious church, but our precious church is for all members.
ውድ “rational Ethiopia" ይህንን ጽሑፍ የጻፈው ዳንኤል እንጂ ማኅበረ ቅዱሳን አይደለም፡፡ ሁለቱን ለማመሳሰል መሞከር የለቦትም ማኅበሩ እንደማኅበር ኤግዚቢሽኑን ያገደው መንግስት ነው አለ እንጂ ፓትርያርኩ አላለም፡፡ የማኅበሩ ድኅረ ገጽ ላይ ገብተው ያንብቡት፡፡ የጅምላ ፍረጃ እጅግ አደገኛ አካሄድ በመሆኑ ከመጻፍዎ በፊት ቆም ብለው ያስቡ፡፡
Deleteዝዋይ ኩንችት ስታበቅል ተመልከቱ
ReplyDeleteኦርቶዶክስ ሆይ እንግድህ ንቃ ለስጋህ ብቻ ሳይሆን ለነፍስህም መኖር አልቻልክም፡፡ማህበረ ቅዱሳን ፈረሰ ማለት ሃይማኖትህ አከተመላት መንጋዎቹም ተበተኑ ማለት ነዉ፡፡ማህበረ ቅዱሳን ባይኖር ኖሮ ለመሆኑ ወጣቶች ይኸን ጊዜ የት ነበሩ ብለህ ጠይቅ፡፡መልሱን ከፊትህ ታገኘዋለህ፡፡ዘረኝነትና ሙስና በተንሰራፋባት ቤተክርስቲያ ዉስጥ ገንዘብ መሰብሰብ እንጅ መንጋዉ የት አለ ብሎ የጠየቀ አባት አለ እንዴ፡፡የለም፡፡ለኦትቶዶክሶች ተብሎ የተከፈተን የቴሌቪን ጣቢያ የሚያዘጋ ፓትሪያርክ እንጅ እንደ ግብጽ ጳጳሳት ቤተክርስቲያን የራሷ ቲቪ እንዲኖራት የሚያደርግ አባት አለ እንዴ፡፡የለም፡፡እረ እንደዉስ አባት ለመባል እኮ ልጆቼ የት ወደቁ አስተዳደጋቸዉስ እንዴት ነዉ፡፡ ምን ተቸገሩ ፤ እኔ አባታቸዉ ምን ማድረግ ይገባኛል ብሎ ሲጨነቅ እንጅ እርሱ ራሱ ጠላት ከሆነ እኮ አባት አይባልም፡፡ክብሩም ብቃቱም የለዉም፡፡የለዉም፡፡ስለዚህ አባትችን ብሎ መጥራትም ተገቢ አይመስለኝም፡፡በመስቀል ባርኩኝ ብሎ ፊቱን ለሚሰጥ ምዕመን ሽጉጥ የሚያወጣ አባት የለም፡፡እነ አቡነ ጴጥሮስ በተቀመጡበት መንበር መቀመጥም ድፍረትና ሃጢያት ይመስለኛል፡፡ስለዚህ ህዝብ ሆይ ፊትህን ለቡራኬ ሳይሆን ለቁጣና ለግሳፄ አዉለዉ፡፡ተቃዉሞህን አሰማ፡፡በሌቦችና በቀማኞች ላይ ጅራፍህን አንሳ፡፡ዝም ብለህ ሃይማኖትህ ትቢያ ስትበላ አትመልከት፡፡
ReplyDeleteየኤግዚቢሽን ማእከልን በተመለከተ የማያደግም እርምጃ መዉሰድ ያስፈልጋል፡፡የገና እና የፋሲካ በዓልን ምክንያት እያደረገ ገንዘብህን ሲግጥ ኑሯል፡፡ከአሁን በሁዋላ ግን ማንም ክርስቲያን ቢሆን ከዘፋኝ አንስቶ እስከ ነጋዴ ድረስ ኤግዚቢሽን ማእከል መግባት የለብንም፡፡እረ እንደዉም በጭራሽ ከአሁን በሁዋላ መግባት የለብንም ፡፡በሚገቡት ነጋዲዎችና ዘፋኞች ላይም የኢኮኖሚ ማእቀብ ማድረግ ይገባናል፡፡እስኪ ለሃይማኖት መቆርቆርን ከሙስሊም ወንድሞቻችንና እህቶቻችን እንማር፡፡ለሰዉ ልጅ ሃይማኖትን፤ትዉፊትን፤ታሪክን እናስተምር ባሉ እንኳንም እሰየዉ መባል ሲገባቸዉ በተንኮልና በሸር ማህረ ቅዱሳን ኤግዚቢሽን እንዳያካሂድ መከልከል እጅግ ትልቅ ንቀትና አምባገነንነተ ነዉ፡፡ከዚህ በላይ ሞት ምን አለ፡፡በተወለድክባት ሀገር ያዉም ኢትዮጵያ ዉስጥ ኦርቶዶክሶች አዉደ ርዕይ እንዳያካሂዱ መከልከል፡፡እረ ማሪያምን በቁም ሙተናል!
.‹‹ሳሩን በልቶ ዉሃዉን ጠጥቶ የተኛዉን በሬ
ቀስቅሰዉ ቀስቅሰዉ አደረጉት አዉሬ›› አለ የሀገሬ አርሶ አደር፡፡
ማህበረ ቅዱሳን ፈረሰ ማለት ሃይማኖትህ አከተመላት መንጋዎቹም ተበተኑ ማለት ነዉ??? የቤተክርስቲያኒቷ ራስ እና ጠባቂ ክርስቶስ እንጂ ማህበረ ቅዱሳን አይደለም፡፡
Deleteዲ/ን ዳንኤል እግዚአብሄር ይባርክህ፡፡ ጸሃፊ ማለት የሚጽፈዉን ነገር በወቅቱና በጊዜዉ የጻፈ ነዉ ጥበበኛም እንደዛዉ፡፡ዉይ ብዕርህ አንጀቴን አርሶታል፡፡ምን ልበልህ ቃላት የለኝም፡፡ ልብ ያለዉ ልብ ይበል፡፡ዳኒ የጻፈዉ ለስድብም ፤ ለሃሜትም ለማስፈራራትም አይደለም፡፡በኢትዮጵያ ምድር ስላለ እዉነታ ነዉ፡፡ዛሬ እዉነቱን ሳይናገሩ በሁዋላ አንድ ነገር ሲፈጠር እንድህ ብየ ነበር ፤እንድህ እንደሚፈጠር አዉቅ ነበር ብሎ ጥግ ጥግን መያዝ አያዋጣም፡፡እዉነትን ተቀብሎ ወደ መፍትሄዉ መፍጠን ነዉ የሚገባን፡፡ዳኒ ተሳድበሃል፤ዘርጥጠሃል ይቅርታ ጠይቅ ማለት ምን ማለት ነዉ፡፡እረ ሌቦቹን ፤ዘረኞቹን፤አይጦቹን አትንካቸዉ መጋረጃዉንም ይቅደዱት መንጋዉንም ይበትኑት ማለት ነዉ፡፡እናንተ የቀን ጅቦች የቤተክርስቲያን መዥገሮች ሁሉ አይዟችሁ በዳኒ ጹሁፍ ከተቀየማችሁ ነገ ከነገ ወዲያ ህዝበ ምእመኑ ወጥቶ በጅራፍ እየገረፈ፤ደማችሁን እየጠጣ ፤አጥንታችሁን እየጋጠ ድራሻችሁን ያጠፈዋል፡፡የማይመታ ልጅ ሲቆጡት ያልቅሳል አሉ!
ReplyDeleteAnonymous zimbel asmesay!!! daniel yerasun hasab enji mahiberun wekilo altsafem! lelaw lib na libuna min malet new? aryos, nistros.... papas neberu gen be nufake timirtachew ende abune mattias kiristosn 2 bahriy bilu(egna ke catholic gar 1 nen bilew) tewegzew teleyu adel? hizbu gen endante aynet dedeb sayhon begilts papasochun tenageru..... endih bilew...... aryos hoy, anten enwedihalen gen timirtihn anwedim new yalut! merz yemirechewn yihen merara afihin legizew zegteh asib...... malete tikikilegna orthodox kehonk..... gen bechirash atmeslim..... tehadiso neger neh!!!!!!
ReplyDelete"በዐውደ ርእዩ የሚማሩት የሚያዩት ብቻ ነበሩ፡፡ አሁን ግን ያላዩትም እንዲማሩ አድርገዋል፡፡"
ReplyDeleteere.........wuuuuuuuuuuuuuuu.........waye waye.............waye...........mine yishlale.................yea tintu nafkigne yeabatotchachine......................THANK YOU .....Dear Daniel
ReplyDeleteDn Daniel: Anjeten new yaraskew, egziabher kante gar new hulem kante gar silehone atfra.
ReplyDeleteI have a better alternative. Keep the church only as a museum, and we need no popes, priests or bishops. We are free men. We don't need any bondage. Religions are social parasites after all.
ReplyDeleteOur church is not a museum and won't be. GOD appointed them because we need them and the church can't stand alone. by the way when you say church that doesn't solely refer to the house but also the assembly of Christians including the ministers. if there are no priests, popes, bishops? who will baptize you, absolve you, help you to repent and take the holy communion ..... think twice such comment is not expected from an Orthodox believer unless you are something else. We should all pray that GOD will change the current situation and we should ask our selves what if our sins made it to happen??? GOD bless our Church.
Deleteይህንን ጽሑፍ ዲ/ን ዳንኤል ክብረት ጽፎታል ብየ ኣላምንም! ሚዛናዊና ታሪካዊ ጽሑፎችን ሲጽፍ የምናውቀው ውድ ወንድማችን፣ እንዴት እንደዚህ ዓይነቱ ድንበር ዘለል (ክርስትያናዊ መንገድን የዘለለ) ጽሑፍ ይጽፋል? ? ? እኔ ኣላምንም!
ReplyDeleteእግዚአብሔር ይጠብቅህ፤ ሌላ ምንም ቃል የለኝም፡፡ ክፉ አይንካህ፡፡
ReplyDeleteme
Deleteከላይ አንድ ወንድም ወይም እህት እንደግለጸ በደቡብ አፍሪካ ቤ/ክ ላይ የተከሰተው ችግር ተመሳሳይ በቬና ኦስትሪያ ቤ/ክ ላይም አሁን እየተፈጸመ እያየን ነው:: ይንሁሉ ችግር የሚፈጥረው ደግሞ ያዎ አጭበርባሪው ተሀደሶዎ የቤተክህነት የውጭ ግንኙነት መምሪያ ፈላጭ ቆራጭ አድርገው ያስቀመጡት አጭቤ ነው:: ከኦስትሪያ ካሉ የተውሰኑ ተሀድሶዎች ጋር በስልክም በአካልም እየተገናኙና በየጊዜው ብር እየተላከለት አሁን ያሉትን እጅግ ቅንና የዋህ ምዕመኑ የሚዎዳቸውን የቤ/ክን አገልጋይ መነኩኔ አንቶ ሌላ ተሀድሶ ለመተካት የሚሰራው ተንኮል እጅግ እጅግ አሳዛኝ ነው:: ሲኖዶስ ምንም ሳያውቅ በሲኖዶሰ ውሳኔ እንደተወሰነ ተደርጎ በፓትርያሪኩ ፊርማ ወጭ እየተደረገ የሚላክ ደብዳቤ ሲታይ እውነትም ሲኖዶሱ ቤተ ክርስቲያኗን ትቷት በዚህ አጭበርባሪው ተሀደሶ የውጭ ግንኙነት ሃላፊ እየተመራች እንደሆነ በግልጽ ያስረዳል:: የቬና ቤተ ክርስቲያን ሰበካ ጉባዔና አገልጋዩ መነኩሴ ለሲኖዶስ ለሚልኩት ደብዳቤና ሪፖርት አንድም ምላሽ አይመጣላቸውም:: በምትኩ ግን ምዕመኑ ምንም የማያውቀው በውሸት የተሞላና የተቀነባበረ የቤተ ክርስቲያኗን አገልጋይ መነኩሴ የሚወነጅል የክስ ደብዳቤ ቤተ ክርስቲያኗን ዘወትር ለሚረብሹ ተሀድሶዎች በግል ይላክላቸዋል:: ይህ የልብ ልብ የሰጣቸው ተሀድሶዎችም የሚፈልጉትን ተሀድሶ አስተዳዳሪ ለማስመጣት የሚችሉትን ሁሉ እያደረጉ ናቸው:: ችግሩና ፈተናው ተዘርዝሮ ስለማያልቅ አቅሙና እድሉ ያላችሁ ምዕመናን ብሶታችንን ለእግዚአብሔርም ለእውነተኛ አባቶችም አቤት በሉልን::
ReplyDeleteEgziabher yistlin
ReplyDeleteI couldn't say more but to say something.
ReplyDeleteDear Daniel, have you read what you wrote? To where the audience you try to lead? Is it to recycle bin? I think you make your fellow beings as football field where you can play. Why don't you advise them to use their mind and time for better? Don't you know that you are going to be liable?
Please correct your errors by erazing them with....
dunzuz neger neh!
DeleteIt is really a shame to find out so many supporters for such an article full of evil. It shows how un mature the young Ethiopian orthodox Tewahedo Church generation really are. The so called Decon Daniel is seeking fame through his tabloid blog and you all are falling for it. May the lord open your inner Eyes and Ears.
ReplyDeleteTrue!!!
DeleteKale Hiwot yasemalin Diakon Dani.
ReplyDeleteውድ ዎንድማችን ዲ/ን ዳን ኤል ክብረት አመሰግንሃለው ምስጋነው ግን የሚያምረው ፍጻሜህ ሲያምር ነው።
ReplyDeletehallo,my dear,great daniel.you made one mistake here, at this time we have not true holly father, they are political leader,at the beginning of the TpLF,they believed that the crack down of orthodox means,the unity of Ethiopia ,specially amhara people has been hammered,as you see from the down-full of derg regime this things had happened, by cleaned the amhare holly fathers,you are not surprising by this because you are a very good,historical ,biblical and political knowledge.you have heard from tplf establisher official told for media, amahra and orthodox church, we have hammered not to raise again.so at this time the Orthodox church has not true holly father,instead they are davel representative.they know how to full their abdomen only.but the people of orthodox they know this truth.God bless you and thank you for this.saint gebireale protecting you from bad things.
ReplyDeleteምነው አሻቅበህ እንዲህ አልከኝ ቢሉ ከመምህሬ ያገኘሁት ነውና እላለሁ!
ReplyDelete