‹‹ዐውቅሃለሁ መሰል››
‹‹ይሆናል፣ የሰው መተዋወቂያው ብዙ ነው›› አልኩት፡፡
‹‹ዳንኤል ነህ አይደል›› አለኝ፡፡ አረጋገጥኩለት፡፡ እኔ በቀን አራት ጊዜ
የሚፈራረቀው የሜልበርን አየር አልገባኝ ብሏል እርሱ ጃቦኒ ነው ያደረገው፡፡ ራሱን አስተዋወቀኝ፡፡ መጽሐፎቼን ማንበቡን
ነገረኝ፡፡ መቼም በውጭ ሀገር ሰማሁ የሚል እንጂ አየሁ፣ እገሌ ነገረኝ የሚል እንጂ አነበብኩ የሚል ሰው ማግኘት ዋድላና
ደላንታ ሄዶ ኦራል እንደማግኘት ብርቅ ነው፡፡ አመሰገንኩት፡፡
‹‹እንግሊዝኛ ብችል ኖሮ አንዳንዱን ጽሑፍ እተረጉመው ነበር›› አለኝ እየሳቀ፡፡
‹‹ታድያ ምን ችግር አለው፡፡ አውስትራልያ የእንግሊዝኛ ሀገር ናት፡፡ ተርጉመው››
አልኩት፡፡
‹‹እንደመጣሁ ቋንቋ ትምህርት ቤት ገብቼ ነበር፡፡ ለስደተኞች የሚሰጥ ኮርስ ስላለ
ለመውሰድ፡፡ እንግሊዝኛና ብስክሌት በልጅነት ካልጀመሩት ጉድ ይሠራል››
ሳቅኩና ‹‹እንዴት?›› አልኩት››
‹‹ሞከርኩትና ቋንቋውን ትቼ ፈገግታውን ብቻ ተምሬው ወጣሁ›› አለኝ፡፡
‹‹የትኛውን ፈገግታ?››
‹‹አለች የእነርሱ ፈገግታ፤ እንደ ፍሬቻ ብልጭ ድርግም የሚያደርጓት፡፡ ቢገባህም
ባይገባህም ከሳቅክ ፈረንጅ ደስ ይለዋል፡፡ ታድያ ሥራ ስገባ ቢገባኝም ባይገባኝም ሳቅ ስል ከአፍንጫ በታች ከአገጭ በላይ በሆነ
ፈገግታ ያጅቡኝ ነበር፡፡ እኔ ደግሞ ሥራዬን ከሠራሁ የእነርሱ እንግሊዝኛ ቢገባኝ ባይገባኝ ብዬ ተውኩላቸው፡፡ አንድ ቀን ግን
ጉድ ሆንኩ፡፡›› ጉጉቴ ከሳቅ ጋር ጨመረ፡፡
‹‹አንድ አብሮኝ የሚሠራ ልጅ አለ፡፡ በጉሮሮ እንግሊዝኛው ሲያወራኝ ስቄ ነበር
የማሳልፈው፡፡ ‹እንግሊዝኛንና ስደትን ስቆ ማሳለፍ ነው› የሚል ጓደኛ ነበረኝ፡፡ ታድያ አንድ ቀን ሥራ እየሠራን የሆነ ነገር
ያወራኛል፡፡ ልብ አልሰጠሁትም፡፡ ሲጨርስ ቀና ብዬ በፈገግታ ሳየው ተናደደ፡፡ በማውቃት እንግሊዝኛ ‹‹ምን ሆንክ›› አልኩት፡፡
‹‹እንዴት እናቴ ትናንት ሞተች ስልህ ትስቃለህ›› አይለኝም፡፡ እኔ ራሴ ደነገጥኩ፡፡ ቀዥቃዣ ፈረንጅ፤ እናቱ ሞታ እስኪ
ከፍራሽ አስነሥቶ ሠለስት እንኳን ሳይደርስ ምን ያመጣዋል፡፡ እኛ ድሮ የተማርነውን ሁሉ አጣመው አጣመው ድምጻቸው ሊያዝልኝ
አልቻለም፡፡ አሁን ሲገባኝ ግን እነርሱ የጉሮሮ እኛ የከንፈር እንግሊዝኛ ነው የተማርነው፡፡››
‹‹ደግሞ እንግሊዝኛ የከንፈርና የጉሮሮ የሚባል አለው?››
‹‹ታድያስ፡፡ እስኪ ስማቸው፡፡ እኛ ‹ዋተር› ብለን ረገጥ አድርገን ስንጠራ እነርሱ
‹ዋር› ብለው በአየር ላይ ያልፉታል፡፡ እኛ ‹ገርል› እየተባልን ጫን ብለን ስንናገር እነርሱ ‹ገ - ል› ብለው በስሱ
ያቆላምጧታል፡፡› አሁን ያለን አማራጭ በአማርኛ እያለቀስን በእንግሊዝኛ መሳቅ ነው፡፡›› እኔ ግን በአማርኛ ሳቅኩ፡፡
‹‹ለምን ትምህርት ቤት አልሄድክም(ውጭ ‹አልገባህም› አይባልም) እዚያ የግድ
ከቋንቋው ተናጋሪዎች ጋር ስትቀላቀል ትለምደው ነበር››
‹‹ድመት ጅራቷ የተቆረጠበት ቦታ ተመልሳ አትሄድም› ሲባል ሰምተሃል፡፡ እኛም
መቀመጫችንን (እርሱ ሌላ ነበር ያለው) የተገረፍንበት ስለሆነ ነው መሰል ወጣ ስትል እዚያ አይመራህም፡፡ እንጂ እዚህ ሀገርማ
ብትማር ብዙ ይረዱሃል፡፡ አየህ ድሮ እንማር የነበረው ለእንጀራ ነበር፡፡ እዚህ መጥተን ሳንማር እንጀራ አገኘን፡፡ ታድያ ለምን
እንማራለን? ደግሞ በየስደተኛው ካምፕ ፀጉራችንንና ልባችንን ጨርሰን መጥተን ነው መሰል እዚህ ሀገር ማስታወስ የሚባል ነገር
የለም፡፡ ቶሎ ትረሳለህ፡፡
‹‹ምን ያህል ጊዜ ቆየህ አውስትራልያ››
‹‹በሃሳብ ዘጠኝ ዓመት፣ በአካል አሥራ ስድስት ዓመት›› አለመረዳቴን ለመግለጥ
አንገቴን ሊወድቅ እንደተዘጋጀ ብርጭቆ አወዛወዝኩ፡፡
‹‹ሱዳን ነበርኩ፡፡ ሱዳን ዘጠኝ ዓመት ቆየሁ፡፡ እዚያ እያለሁ በተስፋ አውስትራልያ
ነበርኩ፡፡ ነገ ትሄዳላችሁ፣ አልቋል፤ ተጠናቋል፤ ፎርም ሙሉ፤ ተዘጋጁ፤ አሻራ ስጡ፤ ፎቶ ተነሡ ስንባል ዘጠኟን ዓመት
ጠጣናት፡፡ እኛስ ይሁን በልጅነታችን ወጥተን ነው፡፡ አረጋውያን አባቶች ነበሩ እዚያ፡፡ ስደትና እብደት ካረጁ በኋላ
አያምርም፡፡ የአብርሃም ቤት አዛውንቶች ሲባል ሰምተሃል?››
‹‹አልሰማሁም›› አልኩት፡፡
ቀጠለ፡፡ ‹‹እነዚህ አዛውንቶች ከ1966 ዓም ጀምሮ በኢዲዩ፣ በከፋኝ፣ በምናምን
እየተደራጁ ሲዋጉ የኖሩ ናቸው፡፡ በኋላ ግን ሁሉም ነገር አልሆን አላቸው፡፡ አረጁ፡፡ መጀመሪያ በተለያዩ ቦታዎች፤ በኋላ ደግሞ
አብዱል ረከም በሚባል የስደተኞች ካምፕ ውስጥ ከሃያ ዓመታት በላይ በሱዳን አሳለፉ፡፡ በመጨረሻም ከዛሬ ሰባት ዓመት በፊት ወደ
350 የሚጠጉ አዛውንቶች አውስትራልያ መጡ፡፡ መንግሥት ጡረታ ይሰጣቸዋል፡፡ ቋንቋው ግን መከራ ያሳያቸዋል፡፡ ቤት የመጣ ፖስታ
ለማንበብ፣ ከማኅበራዊ አገልግሎት ሠራተኞች ጋር ለመግባባት ችግር አለ፡፡ አውስትራልያ ብር እንጂ ቋንቋ አትረዳ፡፡
የዘመድ ሰላምታ ሲመጣ ደብዳቤ
አንብቡልኝ ብዬ ለሰው አስነብቤ - የሚል ዘፈን ትዝ ይልሃል (በዜማ ነው ያለልኝ)
እዚህ ተወዳጅ ዜማ ነው፡፡››
‹‹እዚህ ሀገር ከሱዳን የመጡ ይበዛሉ ልበል፡፡››
‹‹ልክ ነህ፤ በተለይ በኢሕአፓና በኢዲዩ ጊዜ ወጥተው፤አሥርና ሃያ ዓመት ሱዳን ኖረው
የመጡ ናቸው አብዛኞቹ፡፡ ያልተቀየጠ ንጹሕ የኢሕአፓ ዘር እዚህኮ ነው ያለው፡፡ ጓድ ሲባባሉ ትሰማቸዋለህ፡፡
‹‹ ለመሆኑ ግን ከወጣህ በኋላ ወደ ሀገር ተመልሰህ ታውቃለህ?››
‹‹አንድ ጊዜ ብቻ››
‹‹ምነው፤ ጥፊም ይደገማል ይባል የለ እንዴ››
‹‹ታክሲ ነጅ ከሆንክ መደጋገምህ አይቀርም››
ታክሲው አያደርሳቸው››
‹‹ትርፊክ እየጣስክ ትነዳ ትነዳና ነጥብ ትሰበስባለህ፤ ከዚያ ወደ ዘጠኝ አካባቢ
ስትደርስ መንጃ ፍቃድህን ነጥቀው እንዳትነዳ ይሉሃል፡፡ እዚህ ሀገር እንዴት ትዘልቀዋለህ፡፡ ሀገር የናፈቀህ መስለህ ኢትዮጵያ
ትሄድና አንድ ሦስት ወሯን ቅጣት እዚያ ታሳልፋታለህ፡፡ ‹ለዕረፍት የመጣ ፍቅር›› በሚለው ፋንታ ‹ለዕረፍት የመጣ ሾፌር››
የሚል ፊልም ሠርተህ ትመለሳለህ፡፡››
ቢሆንም አገር አይደል››
‹‹ወዳጄ ሀገር ቤት ደርሶ የመጣና ቤቱ የተቃጠለበት አንድ ነው››
‹‹እንዴት››
‹‹ሙልጭህን ነዋ የምትቀረው፡፡ እዚያ ዝንጥ እያለ የምታየው ዳያስጶራ ሁሉ ከሀገሩ
ሲመለስ ስልክ አያነሣ፣ ከሰው አይገናኝ፣ ኢሜይል አይከፍት፤ ይመንናል፡፡ ከሆስፒታል መውጣት በለው፡፡ በተለይ ኢምፖርት
ሊያደርጉ የሚሄዱትማ››
‹‹ምንድን ነው ኢምፖርት የሚያደርጉት››
(ይቀጥላል)
ካሮላይን ስፕሪንግስ፣
ሜልበርን፣ አውስትራልያ
<<እንግሊዝኛና ብስክሌት በልጅነት ካልጀመሩት ጉድ ይሠራል›› የምትመች አባባል ናት፤
ReplyDeleteእያንዳንዱ ንግግርሩ እያሳቀኝ ነው ያነበብኩት በተለይ የሚገልጽበት መንገድ:: in person ደግሞ እንዴት አድርጎ እንደሚያወራው ሳስበው እንደገና ተመልሼ እስቃለህ:: ለማኛውም ደብሮኝ ነበር በጣም አዝናንቶኛል:: ባለበት ምስጋናዬ ይድረሰው ለሰውዬው ላንተም ስላቀረብክልን::
ReplyDeletebetam yazenanal yasetemeralem temechetogal !!!
ReplyDeleteወዳጄ ሀገር ቤት ደርሶ የመጣና ቤቱ የተቃጠለበት አንድ ነው›› Tekekel new !!!
So funny!!!
ReplyDeleteእኔንም ሲያቀብጠኝ እንቅልፌ እንደመጠኝ አነበብኩልህና በሳቅ ፈርሸ ፈርሸ ጠላትህ እልም ይበል እንለፌ እልም አለ፡፡ መሳቅ ብቻ ሳይሆን በሳቅ ፈረስኩልህ፡፡
ReplyDeleteለአንተም ቸር ያሰማህ፡፡
የጣና ዳሩ ነኝ!
‹‹ወዳጄ ሀገር ቤት ደርሶ የመጣና ቤቱ የተቃጠለበት አንድ ነው››
ReplyDeleteI need the whole story soon
ReplyDeletethanks
ReplyDeleteበጣም ነው የሳኩት በጣም ነው ደስ የሚለው። Thanks D.N Daniel
ReplyDeleteስደትና እብደት ካረጁ በኋላ አያምርም፡፡
ReplyDelete”እብደት እና ስደት ካረጁ በኋላ አያምርም፡፡” እውነት ነው!
ReplyDeleteየተረገመ ተራኪ! የተረገመ ፀሐፊ! ! የተረገመ ዕውነት! !!
ReplyDeleteየተረገመ ተራኪ! የተረገመ ፀሐፊ! የተረገመ ዕውነት!
DeleteVery interesting explanation. An explanation that comes from deep love.
DeleteAzenagn ena asetemari shega tshuf Amilak yebarikih abo Danii lanitem erjim edme ke tena gar MEDEHANIALEM yesetlih
ReplyDeleteit is so fanny
ReplyDeletehahaha
ReplyDeleteha ha ha, filfilu gar neber ende yemitawaraw, he seems comedian
ReplyDeleteThank's Deacon Daniel Kibret.
ReplyDeleteስልክ አያነሣ፣ ከሰው አይገናኝ፣ ኢሜይል አይከፍት፤ ይመንናል፡፡ ከሆስፒታል መውጣት በለው፡፡
ReplyDeletenice history & funny
ReplyDeletedenke new yemeketlewn lemanbeb chekolku
ReplyDeleteThen ... / Keziyas ...
ReplyDeleteStill you didn't tell us why you go Australia. Do you live there or for limited time duration?
ReplyDeleteምን ያገባሃል? አሁን ከሞላልህ ጥያቄ ይህን ትጠይቃለህ? እንደዚህ ዓይነት ጥያቄስ በአደባባይ ይጠየቃል?
ReplyDeletelike it.it's so funny!
ReplyDeleteዳኒ አውስትራሊያ ምርጫ ላይ ናት:: እስኪ እግረ መንገድህን የሆነ ነገር በለን::
ReplyDeleteሰላም ላንተ ይሁን የሚገርም ሰው ነው እውነታወችን አዋዝቶ ያለፈበትን ሁሉ አቅልሎ እና ስቆ የሚያሳልፍ ግሩም ስደተኛ ያለንበትን ህይወት በቀልድስላሳያችሁን አመሰግናለሁ ዳኒ ይቀጥል
ReplyDeleteዱኔ የሰውየው አባባል አገርቤት ላለው ወገን ትምሕርት ሰጭ ይመስላል ። ኦጀን እሳት ወስጥ አስገብቸ ካልሞከርኩ አይነት ነገር ካልተፈለገ ።
ReplyDeleteለሁሉም በሰላም ይመልስሕ በርታ።
so so funny and meaning full article
ReplyDeletewhat an habesha living there?
ReplyDeleteአየህ ድሮ እንማር የነበረው ለእንጀራ ነበር፡፡ እዚህ መጥተን ሳንማር እንጀራ አገኘን፡፡ ታድያ ለምን እንማራለን? ደግሞ በየስደተኛው ካምፕ ፀጉራችንንና ልባችንን ጨርሰን መጥተን ነው መሰል እዚህ ሀገር ማስታወስ የሚባል ነገር የለም፡፡ ቶሎ ትረሳለህ፡፡
ReplyDeleteበቅርብ ቀን ለሚከናወነው ለዓለም
ReplyDeleteመጥፋትም ሆነ መዳን ኢትዮጵያ
የመለኮት የፍርድ ምድር
Ethiopia decides the redemption or destruction of the world that is upon us!
Ethiopia is the origin and the salivation of the human race and all creation!
ታድያስ፡፡ እስኪ ስማቸው፡፡ እኛ ‹ዋተር› ብለን ረገጥ አድርገን ስንጠራ እነርሱ ‹ዋር› ብለው በአየር ላይ ያልፉታል፡፡ እኛ ‹ገርል› እየተባልን ጫን ብለን ስንናገር እነርሱ ‹ገ - ል› ብለው በስሱ ያቆላምጧታል፡፡›
ReplyDelete