የሀገርን ክብር ከፍ የሚያደርጉ፣ ጽናትንና ብርታትን የሚሰብኩ፣ አልበገር ባይነትንና
ተጋድሎን የሚያውጁ፣ ለዓላማ ቁርጠኝነትንና ትጋትን የሚናኙ የተባረኩ እግሮች፡፡ ምን ነበር ይሆን የምታስቢው እንዲያ ተከበሽ
ስትሮጭ፣ ምን ነበር ይሆን የምታልሚው እንዲያ ሀገርሽ አንድ ወርቅ እንኳን አጥታ ስሟ ከሠንጠረዡ ሲጠፋ፤ ምን ነበር ይሆን
የምታስቢው የእነ አበበና የነ ማሞ፣ የነ ምሩጽና የነኃሌሌ፣ የነ ቀነኒሳና የነ ገዛኸኝ ታሪክ ወደ ተረትነት ሲለወጥ፤ ተንታኙ
ሁሉ እንዲህ ነበሩኮ የሚለንን ስትሰሚ ምን ነበር ይሆን የምታስቢው፡፡
የሮጥሽውን እንጂ ያሰብሽውን አላየነውም፡፡ ያደረግሽውን እንጂ የወሰንሽውን
አልተመለከትነውም፡፡ ወደየት ነበር የሮጥሽው? ምን ነበር ከፊት የሚታይሽ? አበበ ነው ወይስ ኃይሌ? ባንዲራሽ ነው ወይስ
ሕዝብሽ? መቼም ምንመ ሳታይ እንዲያ አልተፈተለክሽም፡፡ ምንስ ነበር የምትሰሚው? መቼም የሞስኮን ሕዝብ ጩኸት አይደለም፡፡
በማያውቁት ቋንቋ የሚነገር ጩኸት ምች እንዲያ ያስሮጣልና፡፡ ሂጂ፣ ሂጂ፣ ሂጂ ጥሩነሽ ሩጭ፤ ታሪክ ተረት ሆኖ እንዳይቀር
ለሀገርሽ ወርቁን አምጭ› ‹ሂጅ አብረንኅ እየሮጥን ነው፣ ብቻሽን ከቶ አይደለሽም፤ ምሩጽ ቀድሞ ሰባብሮታል፣ ይህ አየር ለኛ
አዲስ አይደለም› የሚለው የሕዝብሽ ድምጽ ነበር በሹክሹክታ የተማሽው? አርምሞኮ ቋንቋ ነው በውስጥ ከነፍስ ጋር የሚያወሩት፡፡
እነዚያ እግሮችሽ እንደ ሲላ ሲወረወሩ፣ እንደ ንሥር ሲበርሩ፣ እንደ አቦ ሸማኔ
ሲፈተለኩ፣ እንደ ሚግ ሲምዘገዘጉ፣ እጆችሽ እንደ መልአክ ክንፍ አየሩን ሲሰነጥቁ፣ ደረትሽ እንደ ሚሳይል እየከፈለው ሲተኮስ፤
እንደታቀፈች ሰጎን ዓይኖችሽ ምድር ምድር ሲያዩ፣ ከአየር ጋር ስትሟገች፣ ከድል ጋር ስትጠራሪ፣ ከእልክ ጋር ተወራርደሽ፣
ከእምቢ ጋር አብረሽ ስትሮጭ፤ ልብና እግሮችሽ ተስማምተው እየተማከሩ ሲነጉዱ፤ ዓይንና እጆችሽ ተፋቅረው የርቀት መጠን ሲለኩ፤
እንደ ንብ አውራ ታጅበሽ፣ እንደ ንብ ንግሥት ስትከንፊ፤ ምነ ነበር ያኔ የምታስቢው?
ሀገር ነበረች ከኋላሽ፣ ሀገር ነበረች ከፊትሽ፤ እንዳንች ማልያ አጥልቀን፣ እንዳንቺ
ሞስኮ ባንጓዝ፤ እንዳንቺ ሀገር ወክለን እንዳንቺ በመም ላይ ባንከፍ፤ ልባችን ካንች ጋር ነበር፣ ሁሉንም ዙር አብሮ ዞሯል፤
ኅሊናችንም ካንቺ ጋር ለአምላክ ሥዕለቱን አቅርቧል፡፡ እንዴት ደስ ይላል መሰለሽ አገር አስከትሎ መሮጥ፤ እያባረርሽን
አልነበረም፣ እየተከተልንሽ እንጂ፣ በእጅሽ መሣሪያ አልያዝሽም፤ ውርደትን ቀዘፍሽው እንጂ፡፡ ሀገርን ሊያኮራ የሚሮጥ፣ ድሮም
ሕዝብ አብሮት ይሮጣል፣ እግሮቹ ብሩካን ናቸው ብሎ ከጥንቱ መርቆታል፡፡ በሞስኮ አፈር ላይ አይደለም በብሩካን እግሮችሽ
የሮጥሽው፣ በሚወድሽና በሚሳሳልሽ ሕዝብ በልቡናቸው ውስጥ ነው፡፡
አብረንሽ ባንሮጥ ኑሮ ድል ስታደርጊ ለምን አብሮ ደስ አለን? ድል አደረግን ሲሉንኮ
አብረናቸው ያልተደሰትን ብዙዎች አሉ፡፡ ድሉ የራሳቸው ብቻ የሆነ፤ ብቻቸውን ያሸነፉ፤ ድላቸውን ያልገዛንላቸው፡፡ አንዳንዶች
ወርቅ ከሀገራቸው ሲያወጡ አንቺ ግን ወርቅ ወደ ሀገርሽ አመጣሽ፤ ስለዚህ አብረንሽ ሮጥን፡፡ አብረንሽም ስለሮጥን አብረንሽ
ተደሰትን፡፡ ሞስኮ ላይ ያዩሽ ሁሉ፤ ምሩጽ አልሞተም አሉ፡፡ አረንጓዴው ጎርፍ ቢደርቅም አረንጓዴ ወርቅ አላቸው አሉ፡፡ ሁሉንም
የሚግባባ ሃሳብና ፕሮግራም፣ አስተዳደርና አመራር፣ አካሄድና መዋቅር በጠፋበት ጊዜ ምሥራቅ ከምዕራብ ሰሜን ከደቡብ አስተባብረሻልና
የመግባቢያ ሰነዳችን ሆነሻል፡፡ በየጎራው የቆሙትን፣ በየተቃራኒው የተሰለፉትን ሁሉንም ሞስኮ አምጥተሸ አንድ አድርገሻቸዋልና
የአንድነት ዓርማ ሆነሻል፡፡
ማጭበርበር በሌለው ምርጫ ተመርጠሻል፤ የምረጡኝ ዘመቻ ሳያስፈልግሽ በተግባር ሕዝብ
አሰልፈሻል፤ ዙፋን ሳያስፈልገሽ ነግሠሽ፣ ሉል ሳያስፈልግሽ ገዝተሻል፡፡ ስም ወደ ግብር ይመራልና ጥሩነሽ ጀግና ሆነሻል፡፡
እግሮችሽን አበርትቶ፣ ጣቶችሽን ያለምልማቸው፣ ኅሊናሽን አንቅቶ፣ ለዓይኖችሽ ብርሃን ይጨምርላቸው፤ የልብሽን ምት ጠብቆ
እጆችሽን አክናፍ ያርጋቸው፤ ሳትደክሚ ምትክሽን፣ ሳታርፊ ደቀ መዝሙርሽን ያሳይሽ፡፡ ቀና እንዳደረግሽን ቀና በይ፣ እንዳከብርሽን
ይክብርሽ፤ እንዳኮራሽን ያኩራሽ፤ እንዳደመቅሽን ያድምቅሽ፡፡
"ቀና እንዳደረግሽን ቀና በይ፣ እንዳከብርሽን ይክብርሽ፤ እንዳኮራሽን ያኩራሽ፤ እንዳደመቅሽን ያድምቅሽ፡፡ "
ReplyDeleteማጭበርበር በሌለው ምርጫ ተመርጠሻል፤ የምረጡኝ ዘመቻ ሳያስፈልግሽ በተግባር ሕዝብ አሰልፈሻል፤ ዙፋን ሳያስፈልገሽ ነግሠሽ፣ ሉል ሳያስፈልግሽ ገዝተሻል፡፡ ስም ወደ ግብር ይመራልና ጥሩነሽ ጀግና ሆነሻል፡፡
ReplyDeleteአርምሞኮ ቋንቋ ነው በውስጥ ከነፍስ ጋር የሚያወሩት፡፡
ReplyDeleteእግሮችሽን አበርትቶ፣ ጣቶችሽን ያለምልማቸው፣ ኅሊናሽን አንቅቶ፣ ለዓይኖችሽ ብርሃን ይጨምርላቸው፤ የልብሽን ምት ጠብቆ እጆችሽን አክናፍ ያርጋቸው፤ ሳትደክሚ ምትክሽን፣ ሳታርፊ ደቀ መዝሙርሽን ያሳይሽ፡፡ ቀና እንዳደረግሽን ቀና በይ፣ እንዳከብርሽን ይክብርሽ፤ እንዳኮራሽን ያኩራሽ፤ እንዳደመቅሽን ያድምቅሽ፡
ReplyDeleteግጥም ነበር ስድ ንባብ ያነበብኩት እሷንም እገዚአብሄር ይባርካት፡፡ አንተንም ጣቶችህን ከቁርጥማት ይጠብቅህ፡፡ እንዴት ዓይነት የተሳለ በዕር ነው
ReplyDeletejegna nesh!!!
ReplyDeleteቀና እንዳደረግሽን ቀና በይ
ReplyDeleteቀና እንዳረግሽን ቀና በይ
ከፍ ከፍ ከፍ በይ
ጸዳል ውበትሽ ሁለቱ እግሮችሽ
ተምዘገዘጉና
ከፍከፍ አሉና
ከፍ አደረጉት ባንዲራውን
ያ የተቃጠለውን ያ የተቀደደውን
yejegna lej jegna new
ReplyDeleteHow ever i like to comment Ethiopian Athletics Federation 1. Why they force athletes with out interest
2. Why they fail to trainee all athletes in group rather than personal managers
Because these are commented for our failure in 10,000 men
Wey Dn Daniel tadleh...simethin meglets tichilaleh!!Egziabher hulachinnm betesemaranbet lewutet yabkan!!
ReplyDeleteእግሮችሽን አበርትቶ፣ ጣቶችሽን ያለምልማቸው፣ ኅሊናሽን አንቅቶ፣ ለዓይኖችሽ ብርሃን ይጨምርላቸው፤ የልብሽን ምት ጠብቆ እጆችሽን አክናፍ ያርጋቸው፤ ሳትደክሚ ምትክሽን፣ ሳታርፊ ደቀ መዝሙርሽን ያሳይሽ፡፡ ቀና እንዳደረግሽን ቀና በይ፣ እንዳከብርሽን ይክብርሽ፤ እንዳኮራሽን ያኩራሽ፤ እንዳደመቅሽን ያድምቅሽ፡፡
ReplyDeleteእጅግ፡ አኮራሽን፡ ጥሩዬ!
ReplyDeleteባንድ፡ ባንዲራ፡ ተቃቅፎ፡ ፎቶ፡ መነሳቱን፣ እና፡ ተመልካቹን፡ እየተዟዟሩ፡ ማመስገኑን፡ ግን፡ ምነው፡ ለኬኒያውያኑ፡ ተውንላቸው? እንደ፡ ጃማይካዊው፡ ቦልት፡ ለብቻ፡ መቦረቅን፡ እነ፡ ሃይሌና፡ እነ፡ ደራርቱ፡ ስላላስለመዱን፡ ጥቂት፡ ግር፡ ብሎኝ፡ አመሸሁ። ሶስት፡ ባንዲራ፡ ይዘው፡ ሶስቱ፡ የኢትዮጲያ፡ ሯጮች፡ ሲታዩ፡ ያልተለመደ፡ ነው። ተቃቅፎ፡ የግል፡ ውጤታማነትንም፡ ሆነ፡ ሀገራዊውን፡ ደስታ፡ መግለጽ፡ እንደዋዛ፡ እየተረሳ፡ መምጣቱን፡ እንደ፡ እኔ፡ እናንተም፡ አስተውላችሁ፡ ይሆን?
መልካም፡ እድል፡ ለቀሪዎቹ፡ ሯጮቻችን!!
Definitely, I was confused for the moment.
Deleteyou are right!
Deletewendme, siyashenfu abro medeset, beruchaw gize keredu athletoch gar sihon yamral.
Deleteአብረንሽ ባንሮጥ ኑሮ ድል ስታደርጊ ለምን አብሮ ደስ አለን? ድል አደረግን ሲሉንኮ አብረናቸው ያልተደሰትን ብዙዎች አሉ፡፡ ድሉ የራሳቸው ብቻ የሆነ፤ ብቻቸውን ያሸነፉ፤ ድላቸውን ያልገዛንላቸው፡፡
ReplyDeleteEnkuan des Yalachihu, all Ethiopians
እግሮችሽን አበርትቶ፣ ጣቶችሽን ያለምልማቸው፣ ኅሊናሽን አንቅቶ፣ ለዓይኖችሽ ብርሃን ይጨምርላቸው፤ የልብሽን ምት ጠብቆ እጆችሽን አክናፍ ያርጋቸው፤ ሳትደክሚ ምትክሽን፣ ሳታርፊ ደቀ መዝሙርሽን ያሳይሽ፡፡ ቀና እንዳደረግሽን ቀና በይ፣ እንዳከብርሽን ይክብርሽ፤ እንዳኮራሽን ያኩራሽ፤ እንዳደመቅሽን ያድምቅሽ፡፡
ReplyDeleteእግሮችሽን አበርትቶ፣ ጣቶችሽን ያለምልማቸው፣ ኅሊናሽን አንቅቶ፣ ለዓይኖችሽ ብርሃን ይጨምርላቸው፤ የልብሽን ምት ጠብቆ እጆችሽን አክናፍ ያርጋቸው፤ ሳትደክሚ ምትክሽን፣ ሳታርፊ ደቀ መዝሙርሽን ያሳይሽ፡፡ ቀና እንዳደረግሽን ቀና በይ፣ እንዳከብርሽን ይክብርሽ፤ እንዳኮራሽን ያኩራሽ፤ እንዳደመቅሽን ያድምቅሽ፡፡
ReplyDeleteእግሮችሽን አበርትቶ፣ ጣቶችሽን ያለምልማቸው፣ ኅሊናሽን አንቅቶ፣ ለዓይኖችሽ ብርሃን ይጨምርላቸው፤ የልብሽን ምት ጠብቆ እጆችሽን አክናፍ ያርጋቸው፤ ሳትደክሚ ምትክሽን፣ ሳታርፊ ደቀ መዝሙርሽን ያሳይሽ፡፡ ቀና እንዳደረግሽን ቀና በይ፣ እንዳከብርሽን ይክብርሽ፤ እንዳኮራሽን ያኩራሽ፤ እንዳደመቅሽን ያድምቅሽ፡፡
DeleteIt is very sad for Ethiopian with out Gold, Thanks for Trunesh Finaly we got one Gold.
ReplyDeleteRunning is also a mind game..ውዳሴ እግር በዛ!
ReplyDeleteHey kine atawkem libel? Lewekesa atchekul!
DeleteWe are waiting for your writing(an article) on mind. I am sure you can't even a reply for a letter.
Deleteቅዱስ ጳውሎስ የግሪክን ባህላዊ ስፖርት አነጻጽሮ ሩጫዬን ፈፀምኩ አለ።
ReplyDeleteወቅቱ የሩጫ ነው። ሁል ጊዜ ኢትዮጲያዊያን የሚሳተፉበትን ሩጫ ስናይ ልባችን ስለምን ይመታል? ይህ የሀገር ፍቅር ሁል ጊዜ ይገርመኛል!
ሩጦ ማሸነፍ ይቆየንና አሯሩጦ ማድከም የቡድን ስራ የት ገባ? ለእናት ሀገሩ መሥዋዕት የሚሆን ማን ይሆን?
ባለፈው ዓመት ለጥሩዬ ከገጠምኩላት የተወሰደ፦
“እውነትም ጥሩነሽ”
(ጥ)ሩነሽ እውነትም ጥሩ ነሽ
(ሩ)ጫን አስተማርሽ አፈትልከሽ ሮጠሽ!
(ነ)ይ ተደሰቺ ባንዲራውን ይዘሽ
(ሽ)ልማትሽ ይህ ነው ለፈሰሰው ላብሽ!
ጥሩነሽ እውነትም ጥሩ ነሽ
እጅግ ይደሰቱ የወለዱ እናትሽ!
ጥሩነሽ እውነትም ጥሩ ነሽ
ይህን ድንቅ ስምሽ ማን ይሆን የሰጠሽ!
ጥሩነሽ እስኪ ልጠይቅሽ
ምነው ቪቪያን ጥለሽ ብቻሽን ገሠገሥሽ!?
እልልልል እኛን ደስ ብሎናል
እጅግ ይደሰቱ የወለዱ አባትሽ!
ጥሩነሽ እውነትም ጥሩ ነሽ
ወርቅ ይዘሽ መጣሽ ለእናት ሀገርሽ!!
http://yonas-zekarias.blogspot.co.uk/
Amen
ReplyDelete5n
ReplyDeleteዳኔ፤ የሾለ ብዕር አለ እንደኔው አድናቄሕ ? ደግ በሉዋል ለዜያውስ ሁል ገብ ። ጥሩነሽንም ሆነ አንተን በሰላም ወዳገራችሁ ትመለሱ ዘንድ ምኞቴ ነው። በርቱ
ReplyDeleteDani le Tirunesh kezihem belay mallet techelalehena tsafelen!! Lezignaw gin enameseginalen! Ashenafi
ReplyDeleteሞስኮ ላይ ያዩሽ ሁሉ፤ ምሩጽ አልሞተም አሉ፡፡ አረንጓዴው ጎርፍ ቢደርቅም አረንጓዴ ወርቅ አላቸው አሉ፡፡
ReplyDeleteሙሉ ጽሁፉን ከእንባ ጋር ጨረስኩት! ማራኪ ነው ዳኒ እግዚአብሔር ይባርክህ!!!
ጥሩዬ ጥሩ ወርቃችን ነሽ፡ በልባችን ጽላት ስምሽን በወርቅ ጽፈሻል እንወድሻለን! ቀና አድርገሽናል አምላክ ዘመንሽን ይባርከው!!!
Amen Dani lantem edimena tena setito yakoyilin
ReplyDeleteእነዚያ እግሮችሽ እንደ ሲላ ሲወረወሩ፣ እንደ ንሥር ሲበርሩ፣ እንደ አቦ ሸማኔ ሲፈተለኩ፣ እንደ ሚግ ሲምዘገዘጉ፣ እጆችሽ እንደ መልአክ ክንፍ አየሩን ሲሰነጥቁ፣ ደረትሽ እንደ ሚሳይል እየከፈለው ሲተኮስ፤ እንደታቀፈች ሰጎን ዓይኖችሽ ምድር ምድር ሲያዩ፣
ReplyDeleteምስጋናችንን ለመግለጽ ከዚህ በላይ ማለት ይቻል ይሆን? አይመስለኝም፡፡
ReplyDeleteሁለተኛ አስሩጠኸናልና ሁለተኛም እንድናመሰግናት አድርገኸናልና አንተንም የንስር ዐይን ይስጥህ
ReplyDeletei like it very much.your hand is blessed and i wish much blessing on your hand.
ReplyDeleteድል አደረግን ሲሉንኮ አብረናቸው ያልተደሰትን ብዙዎች አሉ፡፡
ReplyDeleteማጭበርበር በሌለው ምርጫ ተመርጠሻል፤
የሀገርን ክብር ከፍ የሚያደርጉ፣ ጽናትንና ብርታትን የሚሰብኩ፣ አልበገር ባይነትንና ተጋድሎን የሚያውጁ፣ ለዓላማ ቁርጠኝነትንና ትጋትን የሚናኙ የተባረኩ እግሮች፡፡
ReplyDeletewell said and really she deserves the gold because she was ,is and will remain GOLD
ReplyDeleteEGZIABHER YISTIH ENDEZIH LEHAGERU YEMIKOREKOR BIBEZA YET ABEDERESIN..............
ReplyDeleteቀና እንዳደረግሽን ቀና በይ፣ እንዳከብርሽን ያክብርሽ፤ እንዳኮራሽን ያኩራሽ፤ እንዳደመቅሽን ያድምቅሽ፡፡
ReplyDeleteአንዳንዶች ወርቅ ከሀገራቸው ሲያወጡ አንቺ ግን ወርቅ ወደ ሀገርሽ አመጣሽ፤ ስለዚህ አብረንሽ ሮጥን፡፡
ReplyDeleteDanie God bless Tiruyen and u!nice article
ReplyDeleteሁሉንም የሚግባባ ሃሳብና ፕሮግራም፣ አስተዳደርና አመራር፣ አካሄድና መዋቅር በጠፋበት ጊዜ ምሥራቅ ከምዕራብ ሰሜን ከደቡብ አስተባብረሻልና የመግባቢያ ሰነዳችን ሆነሻል፡፡
ReplyDeleteበየጎራው የቆሙትን፣ በየተቃራኒው የተሰለፉትን ሁሉንም ሞስኮ አምጥተሸ አንድ አድርገሻቸዋልና የአንድነት ዓርማ ሆነሻል፡፡
I can not stop crying! tnx dani
ReplyDeletebe Ewnetim Tiru nat. Tiruwoch hulem Wed Hagerachewin Yitebikalu Degenioch Hulem le Hagerachew Yewdikalu Yenesalu!
ReplyDeleteEgzabher ystlene Truyame Antem Tebreku betme ewdcualuge
ReplyDeleteD/N betikikl yemtimesegen wetat nech ye Ethiopia Nigist bitbalem ayansatim akorachin ye Egziabhier haile keswa gar yehun amen
ReplyDeleteቀና እንዳደረግሽን ቀና በይ፣ እንዳከብርሽን ይክብርሽ፤ እንዳኮራሽን ያኩራሽ፤ እንዳደመቅሽን ያድምቅሽ፡፡ "
ReplyDeleteየሮጥሽውን እንጂ ያሰብሽውን አላየነውም፡፡ ያደረግሽውን እንጂ የወሰንሽውን አልተመለከትነውም፡፡ ወደየት ነበር የሮጥሽው? ምን ነበር ከፊት የሚታይሽ? አበበ ነው ወይስ ኃይሌ? ባንዲራሽ ነው ወይስ ሕዝብሽ? መቼም ምንመ ሳታይ እንዲያ አልተፈተለክሽም፡
ReplyDelete"ሁሉንም የሚግባባ ሃሳብና ፕሮግራም፣ አስተዳደርና አመራር፣ አካሄድና መዋቅር በጠፋበት ጊዜ ምሥራቅ ከምዕራብ ሰሜን ከደቡብ አስተባብረሻልና የመግባቢያ ሰነዳችን ሆነሻል፡፡
ReplyDeleteበየጎራው የቆሙትን፣ በየተቃራኒው የተሰለፉትን ሁሉንም ሞስኮ አምጥተሸ አንድ አድርገሻቸዋልና የአንድነት ዓርማ ሆነሻል፡፡
......
......
......
እግሮችሽን አበርትቶ፣ ጣቶችሽን ያለምልማቸው፣ ኅሊናሽን አንቅቶ፣ ለዓይኖችሽ ብርሃን ይጨምርላቸው፤ የልብሽን ምት ጠብቆ እጆችሽን አክናፍ ያርጋቸው፤ ሳትደክሚ ምትክሽን፣ ሳታርፊ ደቀ መዝሙርሽን ያሳይሽ፡፡ ቀና እንዳደረግሽን ቀና በይ፣ እንዳከብርሽን ይክብርሽ፤ እንዳኮራሽን ያኩራሽ፤ እንዳደመቅሽን ያድምቅሽ፡፡"
Abrensh banrot noro dl stadergi lemn abren tedesetn.
ReplyDeleteDl arederegn silun abrenachew yltedesetn bzuwoch alu.
እግሮችሽን አበርትቶ፣ ጣቶችሽን ያለምልማቸው፣ ኅሊናሽን አንቅቶ፣ ለዓይኖችሽ ብርሃን ይጨምርላቸው፤ የልብሽን ምት ጠብቆ እጆችሽን አክናፍ ያርጋቸው፤ ሳትደክሚ ምትክሽን፣ ሳታርፊ ደቀ መዝሙርሽን ያሳይሽ፡፡ ቀና እንዳደረግሽን ቀና በይ፣ እንዳከብርሽን ይክብርሽ፤ እንዳኮራሽን ያኩራሽ፤ እንዳደመቅሽን ያድምቅሽ፡
ReplyDeleteእግሮችሽን አበርትቶ፣ ጣቶችሽን ያለምልማቸው፣ ኅሊናሽን አንቅቶ፣ ለዓይኖችሽ ብርሃን ይጨምርላቸው፤ የልብሽን ምት ጠብቆ እጆችሽን አክናፍ ያርጋቸው፤ ሳትደክሚ ምትክሽን፣ ሳታርፊ ደቀ መዝሙርሽን ያሳይሽ፡፡ ቀና እንዳደረግሽን ቀና በይ፣ እንዳከብርሽን ይክብርሽ፤ እንዳኮራሽን ያኩራሽ፤ እንዳደመቅሽን ያድምቅሽ፡
DeleteReply
እንዳደመቅሽን ያድምቅሽ!!!!!!
ReplyDeleteSay something for Meseret Defar too, bante yamiral
ReplyDeleteይህንን ብሩህ ጭንቀላትና ያልነተበ ብዕር ከሃያ አምስት ዓመት በፊት ጣና ዳር ላይ ነበር የማውቀው፤ ስላልነጠፈ አምላኬን አመሰግናለሁ! የልቤን ስለገለጽከው ተባረክልኝ ብየሃለሁ፡፡
ReplyDeleteይህንን ብሩህ ጭንቀላትና ያልነተበ ብዕር ከሃያ አምስት ዓመት በፊት ጣና ዳር ላይ ነበር የማውቀው፤ ስላልነጠፈ አምላኬን አመሰግናለሁ! የልቤን ስለገለጽከው ተባረክልኝ ብየሃለሁ፡፡
ReplyDeleteመሰረትን እና ሌሎቹንም ጀግኖች አመስግንልን ብዕር አያያዝህ ስለሚማርከኝ ነው
ReplyDeleteየሚያምር ምርቃት ወድጄዋለሁ
ReplyDeleteWudassie Mariam aynet neger Almeselachuhum?
ReplyDeletewudase jegna new! why dont you do similar achievement for your country and get one for yourself. serto mewedes, sayseru kemewkes yishalal my friend.
DeleteI like it so much! God bless Tirunesh!! Yimiamesegenu brukan nachew ena Danielem egziabher yibarekeh! Amen!!
ReplyDelete"ቀና እንዳደረግሽን ቀና በይ፣ እንዳከብርሽን ይክብርሽ፤ እንዳኮራሽን ያኩራሽ፤ እንዳደመቅሽን ያድምቅሽ፡፡ "
ReplyDeleteReply
ከሯጯ ጸሀፊው እግዚአብሔር ይርዳችሁ፡፡
ReplyDeleteNice coments
ReplyDelete