አሁን ያለንበት ወቅት አብዛኞቹ ትምህርት ቤቶች ተዘግተው ልጆቻችን ቤት ውስጥ መዋል
የጀመሩበት፣ ወይም የክረምት መክረሚያ ነገሮችን ማከናወን የጀመሩበት ጊዜ ነው፡፡ በበጋ ከነበረው የወላጆች ወከባ ዐረፍ
ብለናል፡፡ ልጆችን ትምህርት ቤት ማድረስ፣ የቤት ሥራ ማሠራት፣ ግዙ፣ አምጡ፣ ኑ፣ ሂዱ ከሚሉ የትምህርት ቤቶች ትእዛዞች ዐረፍ
ያልንበት ሰሞን ነው፡፡ አሁን ልጆቻችንን ስለሚመለከቱ ሌሎች ጉዳዮች ለመነጋገር ምቹ ጊዜ ነው፡፡ እኔ ሁለት ጉዳዮችን
መርጫለሁ፤ ዛሬ አንደኛውን እናንሣው፡፡
ጉዳይ አንድ
ባለፈው ሰሞን አንዲት እናት ወደ ቢሮዬ መጥተው እንዲህ አወጉኝ፡፡ ‹‹ልጄ የአሥራ
ሁለት ዓመት ልጅና የ 5ኛ ክፍል ተማሪ ነው፡፡ አልፎ አልፎ የማይበት ጠባይ ግራ የሚያጋባኝ እየሆነ ተቸግሬ ነበር፡፡ ወደ
ትምህርት ቤት ሲሄድ የእኔን ሽቱ ይቀባል፡፡ እኔም ይህን ሳይ የልጅ ነገር አድርጌ ትቼው ነበር፡፡ በኋላ ግን ከሌላው ነገር
ጋር ሲደረብብኝ ነው ግራ የተጋባሁት፡፡ ፀጉሩን እንደ ሴቶች ማስተኛት ይፈልጋል፡፡ ጥብቅ ያለ ሱሪ ካልገዛሽልኝ ይለኛል፡፡
አንድ ቀን ትምህርት ቤት አድርሼው መኪናዬን አዙሬ ልመለስ ስል ከኋላ ያለውን መኪና እንዳልነካው ዞር አልኩ፡፡ ያን ጊዜ
ያየሁትን ነገር ዓይኔ ሊያምን አልቻለም ነበር፡፡ ከአንድ ሌላ ወንድ ልጅ ጋር ከንፈር ለከንፈር ሲሳሳሙ አየኋቸው፡፡ ከኋላዬ
የነበረው መኪና በጡሩንባ እየጮኸብኝ እንኳን የማየውን ተጠራጥሬ ለረዥም ሰዓት ፈዝዤ ነበር፡፡
አንድ ቀን አባቱ ወደ መዝናኛ ቦታ እንዲወስደው ነገርኩትና እኔ ዕቃዎቹን መፈተሽ
ጀመርኩ፡፡ ያኔ ነው የልጄን ጉዳይ በጥልቀት የተረዳሁት፡፡ እኔ ያልገዛሁለት አንድ ቀይ ቲሸርት አገኘሁ፡፡ ቲሸርቱ ላይ
በእንግሊዝኛ ‹I am a gay› የሚል ተጽፎበታል፡፡ ዕንባዬን መቆጣጠር አልቻልኩም፡፡ አልጋው ላይ ተቀምጬ ለረዥም ጊዜ
አለቀስኩ፡፡ ከዚያ በኋላ መቀጠል አልቻልኩም፡፡ ልጄን እንዳጣሁት ገባኝ፤ ልጄን እንደማላውቀው ገባኝ፤ ልጄና እኔ በተለያዩ
መንገዶች እየተጓዝን መሆኑ ገባኝ፡፡
የጓደኛዬ ባለቤት በጉዳዩ ላይ እንዴት ከልጄ ጋር ልወያይ እንደምችል መንገዶችን
አመላከተኝ፡፡ አንድ ቀን ከልጄ ጋር ከአዲስ አበባ ወጣ አልን፡፡ አብሬው ስጫወት ዋልኩና ለሻሂ ዐረፍ ስንል አንድ ስልክ
አነሣሁ፡፡ እንደ ደነገጠ ሰው ሆኜ ነበር የማወራው፡፡ ልጄም ድምፄን እየሰማና ሁኔታዬን እያየ ተደናገጠ፡፡ ስጨርስ ምን
እንደሆንኩ ጠየቀኝ፡፡ ‹‹አንዲት ጓደኛዬ ከባድ ነገር እንደ ደረሰባት፡፡ ልጇ ግብረ ሰዶማዊ እንደሆነባት፡፡ በዚህም ምክንያት
በሕግ ሊጠየቅ መሆኑን›› ነገርኩት፡፡ እጅግ ደነገጠ፡፡ ‹‹የእኔ ልጅ መቼም እንዲህ ያለ ነገር አያደርግም›› ብዬ ተውኩት፡፡
አፍጥጦ ዓይን ዓይኔን ያየኝ ነበር፡፡ ‹‹በጣም ከባድ ነገር ነው የገጠማት፤ ግብረ ሰዶማዊ ማለትኮ በሃይማኖታችንም ትክክል
አይደለም፤ እግዚአብሔር ግብረ ሰዶማውያንን አጥፍቷቸዋል፡፡ ከዚያም በላይ ግብረ ሰዶማውያን በኅሊናቸውም ሆነ በማኅበራዊ
ኑሮአቸው ላይ ችግር እንደሚገጥማቸው፤ ከሕዝቡም እንደሚገለሉ፤ አኗኗራቸውም ከተፈጥሮ ሕግ ውጭ እንደሆነ፤ ወንድ ከሴት ጋር
ሴትም ከወንድ ጋር እንጂ ወንድ ከወንድ፣ ሴትም ከሴት ጋር የሚደረገው ግንኙነት እንስሳት እንኳን የማይፈጽሙት መሆኑን፡፡
የወሲብ ግንኙነት ማንኛውም ወንድ ከ ተፈቀደለት ሴት ጋር ብቻ፣ ባህሉና እምነቱ፣ ሕጉም በሚፈቅደው እድሜና ሁኔታ የሚፈጸም
መሆኑን›› እየዘረዘርኩ መግለጥ ጀመርኩ፡፡ ዝም ብሎ ነበር የሚያዳምጠኝ፡፡ አንዳንድ ሰዎች ልጆቻቸውን ግብረ ሰዶማውያን
እንደሚያደርጓቸው፤ እነዚህ ልጆችም ሌሎችን ልጆች አባብለው ወደዚህ እንደሚያስገቧቸው፤ እንዲያውም ‹I am a gay› የሚል ልብስ የሚለብሱ እንዳሉ ነገርኩት፡፡
ግራ ሳይገባው አልቀረም፡፡ ስለ እርሱ እንደምናገር ገምቷል፡፡ ስጨርስ ‹‹የኔ ልጅ
አንተ ግን እንደዚህ አታደርግም አይደል?›› አልኩት፡፡ ምንም አላለኝም፡፡ ዝም አለኝ፡፡ መሬት መሬት ያይ ጀመር፡፡ ‹‹ምነው
የኔ ልጅ ችግር አለ እንዴ›› አልኩት፡፡ ዝም አለ፡፡ ‹‹አደራህን አንዳንድ ትምህርት ቤቶች ያሉ ልጆች ሌሎች ልጆችን ሳያውቁት
ወደዚህ ነገር እያስገቧቸው ነውና ተጠንቀቅ›› አልኩት፡፡ እሺም እምቢም አላለኝም፡፡ ‹‹አንተ ይህንን ስታደርግ ካየሁ፤ እኔ
ወዲያው ነው የምሞተው›› ስለው ተስፈንጥሮ መጥቶ ጭኔ ላይ ተደፋ፡፡ ሲያለቅስ ይሰማኛል፡፡ ዕንባውም እግሬን ሲያሞቀው
ይታወቀኛል፡፡ እኔም እያለቀስኩ ነበር፡፡
ከብዙ የዝምታ ልቅሶ በኋላ ‹‹እማዬ እኔኮ ጌይ ሆኛለሁ›› አለኝ፡፡ ቀድሜ ባውቅም ያ
ሰዓት ግን መብረቅ የመታኝ ነበር የመሰለኝ፡፡ ከልጄ አንደበት ይህንን ስሰማ ኩምሽሽ ብዬ ትንሽ የሆንኩ መሰለኝ፡፡ የማደርገው ጨነቀኝ፤ ምን ልመልስለት? ምን ልበለው? ግራ ተጋባሁ፡፡ ‹‹ለምን ልጄ? ለምን?››
አልኩት፡፡ ከእኛ ራቅ ብለው የሚያዩን ሰዎች ሁኔታዬ ግራ አጋብቷቸው ሁሉም እኔን ያያሉ፡፡
‹‹እኛ ትምህርት ቤትኮ ብዙ ልጆች አሉ›› አለኝ፡፡
‹‹ምን ምን ታደርጋላችሁ?›› አልኩት
‹‹ሽቱ ተቀብተው ይመጣሉ፤ ደግሞ አንድ ዓይነት ማስቲካ ነው የምንበላው፤ ‹I am a gay› የሚል ቲሸርት እንለብሳለን›› አለኝ፡፡
‹‹ቲሸርቱን ማን ነው የሰጣችሁ?›› አልኩት
‹‹አንድ ልጅ ነው ያመጣልን፤ ለሁላችን ሰጠን፡፡ ግን ከዩኒፎርማችን ሥር
እንድንለብሰው ነግሮናል››
‹‹ሌላስ?››
‹‹ደግሞ አንድ ልጅ የጌይ ፊልም በዕረፍት ጊዜ ያሳየናል››
‹‹የት ነው የሚያሳያችሁ?››
‹‹በኪሱ የሚያመጣው ሞባይል አለ፡፡ እናቴ ናት የምትጭንልኝ ብሏል››
የምሰማውን እንዴት ልመነው?
‹‹እርሱኮ [የልጁን ስም እየነገረኝ] አባቱ ትምህርት ቤት ሲሸኘው ሁልጊዜ ከንፈሩን ይስመዋል›› አለኝ፡፡ ይኼኔ ነቃሁ፡፡
አስታወስኩ፡፡ ሰውዬውንም ዐወቅኩት፡፡ እኔም ደስ አይለኝም ነበር፡፡ አባት ወንድ ልጁን፣ እናትም ሴት ልጇን ከንፈራቸውን መሳም
እዚህ ትምህርት ቤት የማየው ነገር ነው፡፡ ይህ ነገር ልጆቻችን ይህንን መሰሉን ተግባር ከዕድሜ ቀድመው እንዲለምዱት ያደርጋል፡፡
ከዚያም አልፎ ነገ ሌሎች ግብረ ሰዶማውያን በልጆቹ ላይ ይህንን መሰል ተግባር ሲፈጽሙባቸው ምንም እንዳይመስላቸውና የፍቅር መግለጫ
አድርገው እንዲወስዱት ያደርጋቸዋል፡፡ ከባህላችን ያፈነገጡ ነገሮችን
በልጆቻችን ላይ ማድረግ እነዚህ ነገሮች በልጆቻችን ላይ በሌሎች አካላት ሲደረጉባቸው እንዳያስተውሉት እንዳይጸየፉትም ያደርጋቸዋል፡፡
‹‹ለመሆኑ አብራችሁ ስትሆኑ ምን ታደርጋላችሁ?›› አልኩት፡፡
‹‹አንዳንድ ወንዶች ልጆች ይሳሳማሉ፤ እኔ ግን ይደብረኛል፤ ደግሞ ይተሻሻሉ›› አለኝ፡፡ ከገጽታው የመቅፈፍ ስሜት አየሁበት፡፡
ይህንን ስሜት ስመለከት ወደ ችግሩ ውስጥ ዘልቆ እንዳልገባበት ተረዳሁ፡፡ እኔ የማዝነው በባህላችን ተከብሮ የኖረውን የወንድም ለወንድም፣
የእኅት ለእኅት ግንኙነት ግብረ ሰዶማዊነት እያጠፋብን በመሆኑ ነው፡፡ እኔ ከአክስቶቼ ልጆች ጋር አብሬ እየተጫወትኩ፣ አብሬ እየተኛሁ
ነው ያደግኩት፡፡ ልጆቻችን ግን እንዲህ ማድረግ ላይችሉ ነው፡፡ ከአጎታችን፣ ከአክስታችን ጋር መተኛት ለኛ ደስታችን ነበር፡፡ ዛሬ
ግን ዘመዶች በዘመዶች ላይ እንዲህ የሚፈጽሙ ከሆነ ዝምድናችን ሊጠፋብን ነው፡፡ መምህሮቻችንን፣ የሃይማኖት አባቶችን፣ የቤት ሠራተኞችን፣
የጥበቃ ሠራተኞችን እየተጠራጠርን ልንኖር ነው፡፡ ግብረ ሰዶምነት ባህላችንን እጅግ አድርጎ ነው የሚያበላሸው፤ ማኅበራዊ ግንኙነቶቻችንን
ነው የሚበጣጥሰው፤ እንዴት ያለ ችግር ውስጥ ነው የገባነው በእግዚአብሔር?
በኋላ ከአንዳንድ የሕክምና ባለሞያዎች ጋር ስንነጋገር ብዙ ነገር ሰማሁ፡፡ በከተማችን ውስጥ የግብረ ሰዶማውያን ማዘውተሪያዎች የታወቁ
ናቸው፡፡ የራሳቸው የመግባቢያ ‹ቋንቋም› አላቸው፡፡ ትልልቆቹ ግብረ ሰዶማውያን ድራግ በመውሰድ ቀዳሚዎች ናቸው፡፡ እጅግ የሚያሳዝነው
ደግሞ ለሕፃናቱ ድራጉን በከረሚላ መልክ ይሰጧቸዋል፡፡ ከወላጆቻቸው ለመደበቅ ሲሉ ልጆቹ ግለኛነትን ይመርጣሉ፡፡ ከሌሎች ልጆች ወይም
ከዘመዶቻቸው ጋር ከመጨዋት ይልቅ ከጌምና ከቴሌቭዥን ጋር ብቻ መሆንን ይፈልጋሉ፡፡ በተለይም ፌስ ቡክን በሚገባ ለዚህ አስተሳሰብ
ማራመጃ ይጠቀሙበታል፡፡ ወላጆች ኢንተርኔትን ልጆቻችን ያለእድሜያቸው እንዳይጠቀሙበት ማድረግ አለብን፡፡ ስለ ኢንተርኔት አጠቃቀም፣
ስለ ጥቅምና ጉዳቱ ሳንነግራቸው ነው የምንፈቅድላቸው፡፡ ይኼኔ ከበጎው ይልቅ ክፉውን የመያዝ ዕድላቸው ይሰፋል፡፡ በቤታችን ውስጥ
ያስገባናቸውን የቴሌቭዥን ቻነሎችንም መቆጣጠር አለብን፡፡ ልጆቻችን ክፉውንም ደጉንም ዝም ብለው እንዲያዩ ማድረግ የለብንም፡፡ ግብረ
ሰዶምን የሚያበረታቱ ቻነሎች አሉ፡፡
‹አሁን ልጅዎ ከችግሩ በሚገባ ወጥቶልዎታል?›› አልኳቸው፡፡
‹‹ሙሉ በሙሉ ከችግሩ ወጥቷል ማለት አልችልም፤ አሁንም እጠራጠራለሁ፡፡ ፍርሃቱ ገና አልለቀቀኝም፡፡ ነገር ግን ክትትሌን
አላቆምኩም፤ ከልጄ ጋር ያለኝን ቀረቤታም ጨምሬያለሁ፤ ስለ ብዙ ነገሮችም እንነጋገራለን፤ የሃይማኖት ትምህርት እንዲማርም እያደረግኩ
ነው፡፡ አንድ የማውቀው የሥነ ልቡና ባለሞያ ስለ ግረ ሰዶም ጉዳት በሚገባ ነግሮታል፡፡ በተለይ በዚህ ክረምት የተለየ ነገር ለማድረግ
እየሞከርኩ ነው፡፡ ትምህርት ቤቶቻችንን ግን ከትምህርት ጥራትና ከክፍያቸው ባለፈ ወላጆች መከታተል አለብን፤ ልጆቻችንም የተለየ
ነገር ሲያዩ እንዲነግሩን ማሳሰብ ይገባል፡፡ ዘመኑ ወላጅነት ከባድ የሆነበት ጊዜ ነው፡፡ ›› አሉኝ፡፡
ወላጆች ሆይ
እስኪ በጉዳዩ ላይ እንምከርበት፡፡ ከልጆቻችንም ጋር እንነጋገር፤ መምህራን በተማሪዎች ላይ ይህንን ነገር ፈጽመዋል ተብለው
የሚከሰሱበት ጊዜ ላይ ነንና ልጆቻችን እንዳይታለሉ እንንገራቸው፤ ከሃይማኖት፣ ከሥነ ምግባር፣ ከባህል፣ ከጤናና ከማኅበራዊ ኑሮ
አንጻር የሚያስከትለውን ችግር እንንገራቸው፡፡ እኛም ስለዚህ ጉዳይ መረጃ እንዲኖረን እንጠይቅ፣ እናንብብ፣ እንመካከር፤ ከተለያዩ
አካባቢዎች ከምሰማው አንጻር በተለይ በከተሞች ውስጥ ችግሩ ሳይታሰብ ሥር እየሰደደ ነው፡፡ ሰሞኑን የቀረበ አንድ ይፋ ያልሆነ ጥናት
በአዲስ አበባ ከተማ መሰናዶ ትምህርት ቤቶች በሚማሩ 2000 ተማዎች ላይ በተደረገ ጥናት 48% ተማሪዎች የጌይና ሌዝቢያን ደጋፊ
መሆናቸው ታውቋል፡፡ እኒህ እናት እንዳሉት በዚህ ዘመን ወላጅነት ፈተና ውስጥ ገብቷል፡፡ ኃላፊነቱ ሰፍቷል፡፡ መሰናክሉ በዝቷል፡፡
እስኪ የፈጣሪን ርዳታ እየጠየቅን ይህንን ነገር የሰሞኑ የቤተሰብ አጀንዳ እናድርገው፡፡
ዲ/ን ዳንኤል ቃለ ህይወት ያሰማልን፡፡
ReplyDeleteብዙ እንድንዘጋጅ ነው ያደረከን በተለይ ልጆቼን ከንፈራቸውን ስስም በፍቅር ነበር ለካ ግራ ቀኙን ማሰብ ይገባል፡፡
በዚህ በጥፋት ዘመን ከእንደዚህ አይነት መቅሰፍት ይሰውረን፡፡ አሜን፡፡
ጉዳይ አንድ
ReplyDeleteዲ.ን ዳንኤል ያቀረብከው ሃሳብ ወቅታዊ፣ እጅግም አንገብጋቢ ጉዳይ ነው፡፡ነገሩ "ይህች ባቄላ ካደረች..." ነውና ከወዲሁ የሚመለከታቸው አካላት (መንግስት የሃይማኖት ተቋማት ወላጆች እንዲሁም የመገናኛ ብዙሃን) የነገ ሃገር ተረካቢ አበባዎችን ጉዳይ ትኩረት ሊሰጡት ይገባል፡፡ችግሩን ከወዲሁ መቅጨት ካልቻልን ወደፊት ዋጋ ያስከፍለናል፡፡ዘመኑ ሃላፊነት የበዛበት ነገር ግን ሃላፊነቱን የሚወጣ ያነሰበት ዘመኑ መሰናክል የበዛበት ነገር ግን መሰናክሉን ማለፊያ መንገድ የሚያሳይ የጠፋበት ነውና እባካችሁን አበባዎቻችን እንዳይረግፉ በምንችለው አቅም እንረባረብ፡፡ አንተም እግዚአብሄር ያገልግሎት እድሜን ያርዝምልህ፡፡
ReplyDeleteይህ ሊሆን እንደሚችል የታወቀው ዛሬ አይደለም እኮ የመንግስት ድጋፍ ያላቸው መሆኑ የታወቀ ሰሞን ነው:: ይህ ነገር ሀገሪቱ ውስጥ እንዲስፋፋ መንግስት ይፈልገዋል ምክንያቱም ለመንግስት ዳረጎት የሚሰጡት ምእራባውያኑ በ''ምናለበት'' የተሞላና ለሃገሩ: ለባህሉ ደንታ የሌለው ትውልድ እንዲፈጠር ይፈልጋሉ:: የሐይማኖት አባቶች አብዛኛው የህብረተሰብ ክፍል ሐይማኖተኛ ስለሆነ ይህን እናወግዛለን ሲሉ መንግስት እንዳያወግዙ ከለከላቸው:: ጥቂት ወጣቶችም ጉዳዩን በመቃወም ድምጻቸውን ቢያሰሙ እስር ቤት ከተቷቸው:: አፍሪካ ውስጥ በተለይም ኢትዮጵያ ውስጥ ደግሞ የመንግስት ድጋፍ ያለውን ነገር ማስወገድ ፈጽሞ አይቻልም:: ጉዳዩ የሆነ ሰሞን አጀንዳ ይሆናል ከዛ ከንፈር መጥጦና አዝኖ መተው ነው የሚሆነው:: እግዚአብሔር ለትውልዱ ልብ ይሰጥ ዘንድ መመኘት ብቻ ነው መፍትሔው:: መንግስት ፈቃደኛ ሆኖ ለነሱ ያለውን ድጋፍ ቢያቆም ግን በጥቂት ጊዜ ማጥፋት ይቻላል:: መቼም ይህንን ዲሞክራሲ ነው እንደማይል ተስፋ አለኝ:: ለመናገርና ለመጻፍ ዲሞክራሲ ሳይኖረን በሳይንሱም በሃይማትም በየትኛውም መድረክ ተቀባይነት የሌለውን የበከተ ነገር ስለፈቀደ ዲሞክራሲ ሊሆን አይችልም ሌላ ስም ካልተሰጠው በቀር:: ስለዚህ ይህን ነገር ለማጥፋት ከተፈለገ ብቸኛው አማራጭ መንግስት እጁን ከዚህ ጉዳይ ላይ እንዲያነሳና ከኢትዮጵያውያን ሆኖ እንዲቃወም ማድረግ ብቻ ነው:: ያ ካልሆነ ግን እግዚአብሔር በጥበቡ ለትውልዱ ልብን ይስጥ
ReplyDeleteባለፈው ሳምንት በእለተ ቅዳሜ (8/10/2005) ማታ አራት ሰዓት ከሃያ አካባቢ በዛሚ 90.7 በኢትዮፒካሊንክ ፕሮግራም አቅራቢዎች የቀረበው እጅግ አስደንጋጭ ዜና ነው፡፡ አስደንጋጩ ዜና በአንድ ስሙ ባልተጠቀሰ ትምህርት ቤት ውስጥ የ10 እና የ11 ዓመት ወንድ ሕጻናት መደፈራቸው ሲሆን፣ ተጠርጣሪዎቹ ደግሞ የትምህርት ቤቱ ስድስት መምህራን ናቸው፡፡ ልጆቹ በጋንዲ እና በጥቁር አንበሳ ሆስፒታል እንደተረጋገጠው በግብረ ሶዶማዊያን ተደፍረዋል፡፡ ተደፍረዋል የሚለው ቃል የነገሩን ክብደት ያቀለዋል፡፡ ከመግደል ሙከራ በላይ ተዶርጎባቸዋል ብል የተሻለ ይመስለኛል፡፡ በተለይ ነፍስ ያላወቁ ሕጻናት መሆናቸው ለሰሚው ከአስደማሚነት ባለፈ የሚያናድድና ፍጹም ነውረኛነት የተሞላበት ነው፡፡ የአንደኛው ሕጻን እናት የልጇን እና የእሷን ነፍስ ለማጥፋት ሙከራ አድርጋለች፡፡ ይህን ነውረኛ ተግባር ፈጸሙት የተባሉት ስድስቱ ተጠርጣሪ መምህራን ጉዳያቸው በፍርድ ቤት እየታየ እንደሆነም ተገልጿል፡፡
ReplyDeleteግብረ ሰዶማዊነትን (Homosexual) ምንም እንኳ በኃይማኖት አስተምህሮ ውስጥ የታወቀ ቢሆንም ብዙዎቻችንን የፈረንጆች ምናምንቴ ወይም ጣጣ ይመስለን ነበር፡፡ አሁን ግን ዓለምን (አፍሪካን ጨምሮ) እየናጣት ያለ ችግር ሆኗል፡፡ ኢትዮጵያ ውስጥ መነጋገሪያ ከሆነ አመታት ቢቆጠሩም አሁን አሁን እጅግ አሳሳቢ ደረጃ ደርሷል፡፡ ከ21ኛው ክፍለ ዘመን በፊት የተመሳሳይ ፆታ ጋብቻ ውጉዝ ነበረ፡፡ ከአስራ ሁለት ዓመት በፊት ኔዘርላንድ የተመሳሳይ ፆታን ጋብቻ ከፈቀደች በኋላ በተለያዩ ሃገሮች የተመሳሳይ ፆታ ጋብቻ ህጋዊ ሆኗል፡፡ ከእነዚህ ሃገሮች መካከል፡- ፈረንሳይ፣ ቤልጄም፣ አርጄንቲና፣ አይስላንድ፣ ዴንማርክ፣ ብራዚል፣ ካናዳ፣ ስፔን፣ ኖርዌይ፣ ደቡብ አፍሪካ፣ ፖርቹጋል እና ስዊድን ይጠቀሳሉ፡፡ በአሜሪካ እና ሜክሲኮ በዛ ባሉ ግዛቶችም የተመሳሳይ ፆታ ጋብቻ ከተፈቀደ ሰነባብቷል፡፡ ኡራጋይ እና ኒውዝላንድም በቅርቡ የተመሳሳይ ፆታ ጋብቻን ያጸድቃሉ ተብሎ ይጠበቃል፡፡ ከዚህ በተጨማሪም እነ ጀርመን፣ እንግሊዝ፣ ፊንላንድ፣ አንዶራ፣ ሉክሰምበርግ፣ አየርላንድ፣ ታይዋን፣ ኔፓል፣ ስኮትላንድ እና በተለያዩ የአሜሪካ፣ አውስትራሊያ እና ሜክሲኮ ግዛቶች የተመሳሳይ ፆታ (ግብረ ሶዶማዊያን) ጋብቻን ህጋዊ ለማድረግ እየተውጠነጠኑ ነው፡፡ ምዕራባዊያንም ያላደጉ ሃራት የተመሳሳይ ፆታ ጋብቻን መፍቀድ እንዳለባቸው በግልጽ ተናግረዋል፡፡ ይህን የማታከብር ሃገር የሚሰጣት እርዳታ እንደሚጤንባት (እንደሚቀሸብባት ብሎም እንደሚቆምባት) ባደባባይ ዲስኩራቸውን አሰምተዋል፡፡ዊኪሊክስ ከአዲስ አበባ የአሜሪካ ኤምባሲ በተገኜ መረጃ መሰረት፣ ግብረ ሰዶማዊነት በኢትዮጵያ በጣም እንደተስፋፋ ገልጿል፡፡ ከዚህ በተጨማሪም በኢትዮጵያ የሚኖሩ ግብረ ሰዶማዊያን ድህረ ገፅ ወይም ዌብሳይት ከፍተዋል፣ ለምሳሌ www.EthioLGBT.com ፡፡ በተጨማሪም የተለያዩ ማህበራዊ ድህረ ገጾች ላይም ዘመቻውን እያጧጧፉት ነው፡፡ በየትምህርት ቤቱም ሕፃናት በዚህ አስነዋሪ ድርጊት እየተለከፉ ነው፡፡አዲስ አበባ እኮ የወሲብ እብድ ነች፡፡ ያውም እራቁቷን የምትደንስ፡፡ እብድነቷ ደግሞ በተፈጥሯዊ ወሲብ ብቻ እንዳይመስላችሁ፡፡ ከተፈጥሯዊ የፍቅር ስሪያ ባፈነገጡ (በጌዮች እና ሌዝቢያኖች) እየተሞላች ነው፡፡ አንድ ሆቴል ወስጥ የሚሰራ ጓደኛ አለኝ፡፡ ከሚሰራበት ሆቴል የሚገጥሙትና የሚያቸው ነገሮች ግን ይህ ትውልድ ወዴት እያመራ ይሆን ያስብላል፡፡ እጅግም ያስጨንቃል፡፡ እናም ታዛቢው ጓደኛዬ ዛሬ ሌዝቢያኖች መጥተው ነበር፣ ዛሬ ጌዮች መጥተው ነበር፣ ዛሬ አንድ ፈረንጅ አንዲት ሚጥጥዬ ተማሪ ጋር መጥቶ _____፣ ዛሬ አንዲት የምታምር የቤት ልጅ ደላላ ደውሎላት ከአንድ አረብ ጋር አብረው ወደ _____ ሄዱ፣ ይለኛል፡፡ አንድ ቀን “እንዴት ነው ግን ጌዮችን እና ሌዚቢያኖችን የምትለዩአቸው?” ብዬ ጠየቅሁት፡፡ ጓደኛዬ እየሳቀ “ጌዮች እኮ አጓጓዛቸው ብቻ ያሳብቅባቸዋል” አለኝ፡፡ እኔም በግርምት “አጓጓዛቸው ስትል” አልሁት፡፡ አሁንም እየሳቀ “በቃ ሲጓዙ ሸከክ ሸከክ ወይም ሸፈፍ ሸፈፍ ነው የሚሉት” አለኝ፡፡ እኔም እንደመሳቅ ብዬ ሌዝቢያኖችንስ አልሁት፡፡ “እነሱን ማወቅ የምትችለው በሚያደርጉት ድርጊት ነው፡፡ በተለይ ሌዝቢያኖችም ሆኑ ጌዮች ሲጠጡ ማንነታቸው ገሃድ ይወጣል” አለኝ፡፡ ይህ ብቻ ሳይሆን፣ አሁን አሁን ወደ ጭፈራ ቤቶች የሚሄዱት የወንድና የሴት ጥንድ ሳይሆን የተመሳሳይ ፆታ ጥንዶች እንደሆኑ በተለያዩ ሰዎችና መገናኛ ብዘኃን እየተገለጹም ነው፡፡
ታዲያ ትውልድን ለማዳን ምን እናድርግ? ለሚለው ኢ-ተገቢነቱን በህግ ብቻ መከልከል ፋይዳ ያለው አይመስለኝም፡፡ አንድ ቀን ይህ ህግ ሊነሳ ይችላል፡፡ ባይነሳም በምስጢር ዘመቻው ከመስፋፋት የሚያግደው የለም፡፡ እናም እንደኔ ብቸኛው መፍትሔ የሚመስለኝ ትውልድን ማንቃት ነው ብዬ አምናለሁ፡፡ ግደይ በዚህ ጉዳይ ላይ በብርቱ መጻፍ ያለብህ ይመስለኛልSOURCE= http://www.geezbet.com/2013/06/blog-post_29.html
ይህን ፅሁፍ በ 30/10/05 የፍርድ ቤት ውሉቸወን ሪፖረተር ላይ አንብቢለሁ ጊን በቃ ሊዋጥልኝ አለቻለም አንድ እናት ልጃ ተደፍሪለሁ እያላት ሞባይል ሰጥቶ ሲነኩህ ደወልልኝ ማለት ሱሪውን ከቲሸርቱ ጋር ሰፍቶ መላክ ምን ማለት ነው ድርጊቱን ለወላጆቹ ከወቁ የዛኑ ለት ለምን ወደ ፖሊስ ሪፖርት አላደረጉም አንድ አይነት 6 መምህራን ባንድ ት/ቤት ወስጥ ይህን ሁሉ ጉድ ሲፈጽሙ ሃይ የሚል አንድ ደህና ሰው ጠፋ ወይ ያሁሉ ተማሪ ባለበት ጊቢ ወስጥ ሱሪ ተወልቁ ይህ ሁሉ ጉድ ሲፈጸም ያየ አንድ ተማሪ እንዲት ጠፋ የሁለቱ ልጁች እናቶች እነዲት ሊተዋወቁ ቸሉ አላውቅም አንዳንዲ የጥቅም ግጪቶች የሚመስል ነገር አለው የሂ በልጁቹ ላይ የውነት ተደርጎ ከሁነ መምህራኑ በቻ ሳይሁን ሰምተው ዝም ብለው ወደ ት/ቤት ሲልኩ የነበሩ ወላጆችም ለፍርድ ሊቀርቡ ይገባል፤፤
Deleteከተለመደው የማኅበረሰቡ ወግና የአኗኗር ዘይቤ ወጣ ያሉ፣ ግለሰባዊ ሰብዕናንና ክብርን የሚፈታተኑ፣ የኢትዮጵያዊነት እሴቶችን የሚያወርዱና የሚያጠፉ የቀንና የሌሊት ጭፈራ ቤቶች፣ የእርቃን ጭፈራ ቤቶችና ግብረ ሰዶማዊነት በከተማው ውስጥ መስፋፋታቸው እጅግ አሳሳቢ ደረጃ ደርሷል፡ የተመሳሳይ ጾታ የወሲብ ግንኙነት/ግብረሰዶማዊነት/ን በተመለከተ በተገኘው መረጃ፣ ተፈጥሮአዊ ከሆነ የተራክቦ ተግባር የተለየና ያፈነገጠ፣ ተግባሩም ከእምነት፣ ከባህል፣ከሥነ ምግባርም ሆነ ሞራል (ግብረገብ) አንጻር ብዙ ድጋፍ የሌለው ቢሆንም ድርጊቱ የተስፋፋ በ ማህበረሰቡ ላይ የስነ ልቦና ፤ ማህበራዊ ግንኙነት ችግር ትምህርት ማቐረትና የጤና ድርጊቱ የተስፋፋ በ ማህበረሰቡ ላይ የስነ ልቦና ፤ ማህበራዊ ግንኙነት ችግር ትምህርት ማቐረትና የጤና ችግር ዕድሜያቸው ከ15 ዓመት በታች የሆኑ ሕጻናት ተማሪዎች፣ የሁለተኛ ደረጃና የከፍተኛ ተቋማት ተማሪዎች፣ በወሲብ ንግድ ሥራ የተሰማሩ ሰዎች፣ እንዲሁም በማረሚያ ቤት የሚገኙ የሕግ ታራሚዎች ከፍተኛ ተጠቂዎች ናቸው፡፡በጥናቱ ከተገኘው ሌላ መረጃ ለመረዳት እንደተቻለው በአሁን ጊዜ ለየት ያሉ ተግባራት የሚፈጸሙባቸው መታሻ/ማሳጅ ቤቶችን መጠቀም እየተለመደ የመጣ አዲስ ልምድ ሆኗል፡፡ መታሻ ቤቶች የሚገኙባቸውን አካባቢዎች ለመለየት በተደረገው ቅኝት ለማወቅ እንደተቻለው፣ ብዙዎቹ ደረጃቸውን የጠበቁ ትልልቅ የመኖሪያ ቤቶች ውስጥ ሲሆኑ፣ ሌሎች ደግሞ በትልልቅ የንግድ ሕህንፃዎች ላይ የተከፈቱ ናቸው፡፡ ይሁን እንጂ በምልከታው ወቅት በተደረገ ኢ-መደበኛው ውይይት እነዚህ ቤቶች እንደ ማንኛውም ሥራ ፈቃድ ያላቸውና አንዳንቹም ሃያ አራት ሰዓት የንግድ ቤቶች መሆናቸው የታወቀ ሲሆን፣ በነዚህ ቤቶች ውስጥ ወሲብ ነክ ድርጊቶች የሚፈጸምበት አሰራር መኖሩንም ለማወቅ ተችሏል፡፡ ቤትክርስትያን ውስጥም ገብቷል የዝዋይ ገዳም ችግርን ያስታውሷል!ቤትክርስትያን ውስጥም ገብቷል የዝዋይ ገዳም ችግርን ያስታውሷል!
ReplyDeletethe one who miss his line
ReplyDeleteዲ/ዳንኤል ቃለ ሕይወት ያሰማልን በእድሜና በጤና ይጠብቅህ ሊታሰብበት የሚገባ ጉዳይ ነው
Deleteቃለ ህይወት ያሰማልን
ReplyDeleteሊታሰብበት የሚገባ ጉዳይ ነው
Deakonne Danel Egzabher yebarkhe gen yenge abeboche gudie betme asasby ejone mettoal murate memekaker alebene mensha hasbe endhone ande neger letkume semonune 12 kefel fetna yechersu tmaroche asphelt moltewe eyecheferu be 5kilo syalfe menden new beye setyeke yemnelke temarwoche nachew tbalku weye gude bye segerm k4kilo wed mexico bmyamer taxi west hojae ande fetaje ena tefetaje tegnjetwe lejocho endat honu sebablu joroyene sekcha sadamet s.o.s kefteja derja temeret bet yalu temarwche degmo uniform sebesbew maqtelachewen yehenenem bvido skersu police meto endbetnew semu leba betme azene zare yene sesema betme lebe dema era gobeze enmekaker teweld menged eyesate aktacha eyetfabet new bteloste bemetfe belene lejochacenen enetadege
ReplyDeleteGod know what you are trying to say bro
Deleteይህንን፡ የመወያያ፡ ርዕስ፡ በማንሳትህ፡ ፈጣሪ፡ አብዝቶ፡ ይባርክህ-ልጆችህን፡ ይጠብቅልህ።
ReplyDeleteከዚህ፡ ቀደም፡ በተደጋጋሚ፡ እንዳነሳኸው፡ የዘመናችን፡ ትልቁ፡ አደጋ፡ የቴሌፎንና፡ የኢንተርኔት፡ ቴክኖሎጂ፡ ሲሆን፡ ይህ፡ በራሱ፡ እጅግ፡ ጠቃሚና፡ ጉዳት፡ የሌለው፡ ቢሆንም፡ አጠቃቀሙን፡ ባለማወቅ፡ የሚረባውን፡ ከማይረባው፡ ሳንለይ፡ ራሳችንንና፡ የራሳችን፡ የሆኑትን፡ እየጎዳንበት፡ እንገኛለን። ማንም፡ ወላጅ፡ የልጁን፡ ነፃነት፡ ባይገድብ፡ ይመርጣል። የቴሌፎን፡ ተጠቃሚ፡ ቢያደርገው፣ ኢንተርኔት፡ እንዲያይ፡ ቢፈቅድለትና፡ ሁኔታዎችን፡ ቢያመቻችለት፡ እና፡ ሌሎችንም፡ አቅሙ፡ የሚችለውን፡ ሁሉ፡ እያደረገ፡ በፍጹም፡ ነጻነት፡ ቢያሳድግ፡ የማይወድ፡ የለም። ነገር፡ ግን፡ እንደ፡ ወላጅ፡ የማይጠቅመውን፡ ከሚጠቅመው፡ የመለየት፡ ሃላፊነቱ፡ በእኛ፡ በወላጆች፡ ላይ፡ የተጣለ፡ ስለሆነ፡ የነፃነት፡ ገደቡን፡ የማበጀት፡ ድርሻ፡ አለብን። የወላጅ፡ ጭንቁ፡ ታዲያ፡ የልጁ፡ እኩዮች፡ ያገኙት፡ የርሱ፡ ልጅ፡ ግን፡ ያላገኘው፡ ነገር፡ እንዳይኖር፡ ነው። ወላጆች፡ ደግሞ፡ እርስ፡ በርስ፡ ስለማይተዋወቁ፡ የልጆችን፡ ጥያቄ፡ ብቻ፡ መሰረት፡ እያደረጉ፡ "ልጄ፡ ከጓደኞቹ፡ ቢያይ፡ ነው፡ ይህንን፡ የጠየቀኝ፤ ባላደርግለት፡ ያዝንብኛል፤ የበታችነት፡ ስሜት፡ ያድርበታል" እየተባለ፡ አላስፈላጊ፡ ነገሮች፡ በሽሚያ፡ ሲደረጉ፡ ማየት፡ የተለመደ፡ ነው። በቂ፡ መረጃ፡ ቢኖር፡ ግን፡ ማንም፡ ወላጅ፡ ልጁ፡ የማይጠቅመውን፡ ነገር፡ ማድረግ፡ ባልፈቀደም፡ ነበር። ስለዚህ፡ እንደ፡ አንድ፡ መፍትሄ፡ ብዬ፡ የማቀርበው፡ በየትምህርት፡ ቤቶች፡ ያሉትን፡ የወላጆች፡ ማህበራት፡ ማጠናከርና፡ ስለልጆቻችን፡ የምንወያይባቸውን፡ መድረኮች፡ ማስፋት፡ ይመስለኛል። ብዙ፡ ጊዜ፡ እንደታዘብኩት፡ ግን፡ እንዲህ፡ ያሉት፡ ማህበራት፡ በወላጆችም፡ ሆነ፡ በትምህርት፡ ቤቶች፡ በቂ፡ ትኩረት፡ የማይሰጣቸው፣ በዓመት፡ አንድ፡ ጊዜ፡ ለወላጆች፡ ቀን፡ ብቻ፡ ፋይዳቸው፡ ተተምኖ ፡ የተቀመጡና፡ ለይስሙላ፡ የሚቋቋሙ፡ ናቸው። ይህ፡ ሊታረም፡ ይገባል። ዛሬ፡ በሥራ፡ ብዛት፡ በማሳበብ፡ አሊያም፡ ሀላፊነትን፡ መበሸሽ፡ ከእንዲህ፡ ያሉ፡ ማህበራት፡ ብንርቅ፣ ወይም፡ ለመጠናከራቸው፡ አስተዋጽኦ፡ ባናደርግ፡ ነገ፡ ችግሩ፡ በራችንን፡ ሲያንኳኳ፡ ሥራችንን፡ ብቻ፡ ሳይሆን፡ በታሪኩ፡ እንዳየነው፡ የምንሳሳላቸውን፡ የትውልድ፡ ተረካቢ፡ የሆኑትን፡ ልጆቻችንንም፡ እናጣቸዋለን። "አለባብሰው፡ ቢያርሱ፡ ባረም፡ ይመለሱ" እንደተባለው፡ ችግሩ፡ እስኪደርስብን፡ ልንጠብቅ፡ አይገባም።
ሌላው፡ በየቤታችን፡ ያለው፡ የልጆች፡ አያያዝም፡ መፈተሽ፡ ይኖርበታል። የልጆች፡ መኝታ፡ ቤት፡ እየተለየ፣ እያንዳንዱ፡ ልጅ፡ የራሱ፡ ክፍል፡ በነፍስ፡ ወከፍ፡ እየታደለው፡ የሚያድግበት፡ ዘመን፡ ላይ፡ ደርሰናል። አብሮ፡ መተኛትና ቤተሰባዊ፡ መቀራረብ፡ እየጎደለ፣ ግለኝነትን፡ ገና፡ ከልጅነት፡ እያስተዋወቅናቸው፡ ነገሮች፡ ከቁጥጥር፡ ውጭ፡ እየሆኑ፡ "do not disturb" የሚል፡ ማስታወቂያ፡ በራሳችን፡ ቤት፡ ውስጥ፡ የልጄ፡ መኝታ፡ ቤት፡ ባልነው፡ በር፡ ላይ፡ እየተለጠፈብን፣ ለሚፈጠረው፡ ችግር፡ መፍትሄ፡ ማግኘት፡ በጣም፡ ከባድ፡ ነው፡ የሚሆነው። ስለዚህ፡ እስቲ፡ የቤት፡ አስተዳደራችንንም፡ እንፈትሽ። ቤታችን፡ ልጆቻችን፡ እርስ፡ በርሳቸው፡ የሚያቀራርብ፡ እንጅ፡ የሚያለያይ፡ ቤት፡ አናድርገው። ከፍ፡ ሲሉ፡ ሴቶችን፡ ከወንዶች፡ መለየት፡ ተገቢ፡ ቢሆንም፡ ተመሳሳይ፡ ጾታ፡ ያላቸውን፡ እስቲ፡ አንለያያቸው። እርስ፡ በርሳቸው፡ በሚኖራቸው፡ መቀራረብ፡ ከምንጠብቀው፡ በላይ፡ ራሳቸውን፡ የሚጠቅሙ፡ ሲሆን፡ ከእነርሱም፡ አልፎ፡ ደግሞ፡ እረፍቱ፡ ለእኛ፡ ነው። እንዳይበዛብኝ፡ ሃሳቤን፡ እዚሁ፡ ባጭሩ፡ ልግታው።
ፈጣሪ፡ መልካሙን፡ ያሰማን።
ዘመኑ ወላጅነት ከባድ የሆነበት ጊዜ ነው፡፡ thank you.
ReplyDeleteመንግስታችን የፑቲንን እርምጃ ቢጠቀም መልካም ነው
ReplyDeleteይህን ርእስ በማንሳትህ ደስ ብሎኛል አሁን አሁንስ ብዙ ነገሮቸ እየገረሙኝ ነው አሁን ካነሳኽው ጉዳይ አንጻር ሲመዘን የሚዲያ ሰዎቻችን ሲመላለሱበት የሚውሉበት ርእስ ምንም ትርጉም የለሽ እየሆነብኝ ነው ምክንያቱም አሁን በቅርቡ እንኳን በአሜሪካ አንዳንድ ግዛቶች የተመሳሳይ ፆታ ጋብቻ መፈቀዱን አስመልክቶ የተለያዩ የመረጃ ምንጮች ብዙ እያሉ ነው ለምንድነው ታዲያ የኛ ሚዲያዎች ሰለዚህ አስነዋሪ እና ትውልድ ገዳይ ጉዳዩ ለማውራት ያልደፈሩት ድርጊቱን ከነቀፍነው አድማጭ እናጣለን ብለው አስበው ነው እንዴ ህሊናችንን እያረከስን ስለሆዳችን ብቻ የምንጨነቅ ከሆነ ይሄ ርኩስነት ነው እነርሱም ጉዳዩን የሚደግፉት ከሆነ እንደግፈዋለን ብለው ይሄንን ቅጥ ያጣ የዲሞክራሲ ዲስኩራቸውን ይንፉብን በዚህ ጉዳይ በቅርቡ ባራክ ኦባማ ይቅርታ ፕሬዝዳንት የሚለውን ረስቼው እንዳይመስላችሁ ስለረከሰብኝ ነው የተውኩት በዚህ ጉዳይ አስተያየቱን ሰጥቶ ነበር ምን አለ መሰላችሁ እኩልነት ሲረጋገጥ በማየቴ ደስ ብሎኛል ወንድና ሴት እንዲጋባ እንደተፈቀደ ሁሉ ተመሳሳይ ፆታውን ለማግባት የሚፈልግም መብቱ ሊከበርለት ይገባል ብሏል አዬ ዲሞክራሲያዊነት አሁንስ የዲያቢሎስ ስራ አስፈፃሚዎች ስራቸውን እያከናወኑ እንደሆነ እየገባኝ ነው በርትተን እንፀልይ ባገኘነው አጋጣሚ ሁሉ ይሀንን መጥፎ የጥፋት ተግባር እናውግዝ ይሄንን ያላዩ አባቶቻችን እና እናቶቻችን ምን ያህል የታደሉ ናቸው ለዛሬው ይብቃኝ ደህና ሁኑ ዲያቆን ዳኒ በደንብ እንነጋገርበት ጉዳዩን ትኩረት ስጠው ላሁኑም ቢሆን እግዚአብሄር ይባርክህ
ReplyDeleteወዳጄ ዳንኤል፤ ጥሩ ነው ነገር ግን ቁስሉን ፈርቶ ንፍፊቱን ማከም አይሆንብህም! የችግሩን ምንጭ እስካላጠራን ድረስ፤ የችግሩ መገለጫ መወያየት፤ ዉሃ ቢወቅጡት እምቦጭ ነው። መጀመሪያ ለዜጎቹ ግድ የሚለው አስተዳደር አገራችን ያስፈልጋታል። ይህ ሲሆን፤ የሚከሰቱትን ችግሮች ለመቋቋም የሚያስችል ህግ በማውጣት ተፈጻሚ ማድረግ ይቻላል። ካልሆነ ግን ለራሱም ሆነ ላገሩ ዴንታ የሌለው ዜጋ የመፍጠሩ ስራ ይቀጥላል። እኛም እንዲሁ!!!
ReplyDeleteቤተክርስቲያን ልጆቿን መያዝስ አላፊነት የለባትም?
ReplyDeleteeh, tewat tegnitalech. God will ask the so called Religious leaders at the day of judgement. I wish I hear the conversations b/n God & them.
DeleteHahaha... manat yetegnach? betekirstian mechem atitegnam!!! yetegnaw sew new. betekiristian huliem tastemiralech.....
DeleteAre u sure, altegnachim?. Usually when I go to church, I don't know, the way it is preached does not attract me. It is not the same with the time of our fathers & mothers. I think we are totally d/t b/c of effect of modernization. Don't think there should be d/t strategy to adress us, that is why I said " tegnitalech"
Deletele hagerna lewegen maseb yih newu egziabher yibarikih
ReplyDeletethanks a lot dani.....please inform it for all concerned gov't agency's . its really the profound problem for our community ....death penalty for those who are misleading under age kids.
ReplyDeleteOH MY GOD....MINEW EME BRHAN.....!!!!!
ቀን ይህንን አንብቤ ማታ ከባለቤቴ ጋር ተወያየንበት፡፡
ReplyDeleteለባለቤቴም ፅሁፉን አስነበብኳት፡፡ ይህ ጉዳይ ሁሉም ወላጆች ሊወያዩበት የሚገባ ጉዳይ ነው፡፡
ባለቤቴ ብዙ ነገር አጫወተችኝ፡፡
አንድ ጊዜ የልጆቼ ሰርቪስ ሹፌር ለልጄ አዲስ ደብተር ገዝቶ ይሰጠዋል እና ባለቤቴ በጣም ተናደደች፡፡ ምንድነውና እሱ የሚገዛው እኛ ግዛልን ብለነዋል ብላ ገንዘቡን ላከችለት ልጄንም ሁለተኛ አንድ ነገር ትቀበልና ብላ አስጠነቀቀችው እኔ ግን ብዙም ትኩረት አልሰጠውትም ነበር፡፡ በጣም በቅን ልቡና ለተማሪዎቻቸው ጥሩ ሽልማት የሚሰጡ የሰርቪስ ሹፌሮች ቢኖሩም ግራ ቀኙን ግን ማየት እንደሚገባኝ ተማርኩበት፡፡
ባለቤቴም ስትነግረኝ
አንዷ እናት ታክሲ ውስጥ የ3 ዓመት ልጇን ይዛ ትገባና ቦታው ስላልተመቻት ውሥጥ ካሉት ተሳፋሪዎች አንዱ አምጫት እኔ ጋር ይልና ይቀበላታል፡፡ ጭኑም ላይ ያስቀምጣታል፡፡ ታዲያ ሰውየው የሰይጣን ፈረስ ነበርና እያሳሳቀ እያሻሸ ፓንን አውልቆ ቀበቶውን ፈትቶ ሰው መሓል በጠራራ ፀሐይ እና ያለችበት ለዚያውም ታክሲ ውስጥ አስፀያፊ ተግባሩን ለመፈጸም ይሞክራል፡፡ በዚህ ጊዜ ልጅ ስትጮህ ሁሉም ተደናግጦ እናት ልጇን ስትቀበል የሚያሳዝነውን ተግባር ትመለከትና ኡኡ ትላለች፡፡ ሁሉም ተረባርቦ ወደ ህግ ያመራሉ፡፡
ይህ አጋንንት ምን ያህል እንደሰለጠነ የሚያሳይ ነው፡፡
በየሆቴሉ ወንድና ወንድ ሴትና ሴት ተያይዞ መግባት በሰው ፊት ከንፈር ለከንፈር መሳሳም የተለመደ እሆነ እንደመጣ ስራ ቦታዋም ብዙ ነገር እንደሰማች ተጨዋወትን፡፡
ይህንን ጉዳይ ከስራ ባልደረቦቼም ጋር ተወያየንበት፡፡
ከስራ ባልደረቦቼም ብዙ ነገር ሰማሁ፡፡ አንዳንድ ጊዜ ሰራተኞች እንኳን ታዳጊ ህፃናት የማያውቁትን ጉዳይ ካለ እድሜያቸው እንደሚያሻሹአቸውና መጥፎ ተግባር ለመፈም እንደሚሞክሩ አጫወቱኝ፡፡ ወንዶችንም አስገድደው እየደፈሩ እንደሆነ ሰማሁ፡፡
ወላጆች ሆይ
1ኛ. ማንም ሰው እናዳያሻሻቸው በከረሜላ በማስቲካ እንዳያባብላቸው ማስጠንቀቅ
2ኛ. በተቻለ መጠን ልጆች በሰ/ት/ቤት ቃለ እግዚአብሔር እንዲማሩ ማድረግ
3ኛ. ውሎአቸውን መጠየቅና መከታተል፡፡ አስተማሪ እንኳን መቅጣት ቢፈልግ በአግባቡ መሆን እንዳለበት ማስተማር፡፡
4ኛ. መቼም 8ኛ ሺህ ሊፈፀም ነውና ፈጣሪ ከእንደዚህ አይነት መዓት ልጆቻችንን እንዲሰውርልን ተግተን መማፀን ይገባል፡፡
እኔ በተቻለ መጠን ለፌስ ቡክ ጓደኞቼ ሁሉ ሼር አድርጌ ሃሳባቸውን እንዲሰጡበት ጠይቄአለሁ፡፡
በተረፈ ሁላችንም ብንወያይበትና ገጠመኞቻችንን እንዲሁም የሰማነውን ብንፅፍ መልካም ነው እላለሁ፡፡
ዲ/ን ዳንኤል እድሜና ጤና ይስጥልን፡፡ ይህንን ጉዳይ ግን በደንብ አስበህበት በድረ ገፅህ ብቻ ሳይሆን በአካልም እንድንወያይበት መላ ብትል፡፡
ቸር ይግጠመን፡፡
Ye kidus abat I like your concern.Your wife is lucky.
DeleteIm so scared ... scared to be d mom of dis generation :(((
Deleteበአሜሪካ በግልጥ ተፈቅዶላቸዋል፡፡ ፕሬዝዳንቶች የራሳቸውን እድሜ ለማራዘም የስንቱን ሕይወት እንደሚያበላሹ ተመልከቱ፡፡
ReplyDeleteይህንን በገሃድ የፈቀደውን
ኦባማ
ዶማ
ብዬዋለሁ!!!
ሁለታችሁንም ማለቴ ተሞክሮዋን ያካፈለችው ወላጅና በመፅሄት ያወጣችሁትን እግዚአብሄር ይባርካችሁ እግዚአብሄርን በእጅጉ የሚያስቆጣውና ለማይረባ አዕምሮ ተላልፎ የመሰጠት ውጤት መሆኑን በሮሜ ምዕ1 ከቁ 24 እስከ 28 እንዲህ ይላል
ReplyDelete24
ስለዚህ እርስ በርሳቸው ሥጋቸውን ሊያዋርዱ እግዚአብሔር በልባቸው ፍትወት ወደ ርኵስነት አሳልፎ ሰጣቸው፤
25
ይህም የእግዚአብሔርን እውነት በውሸት ስለ ለወጡ በፈጣሪም ፈንታ የተፈጠረውን ስላመለኩና ስላገለገሉ ነው፤ እርሱም ለዘላለም የተባረከ ነው፤ አሜን።
26
ስለዚህ እግዚአብሔር ለሚያስነውር ምኞት አሳልፎ ሰጣቸው፤ ሴቶቻቸውም ለባሕርያቸው የሚገባውን ሥራ ለባሕርያቸው በማይገባው ለወጡ፤
27
እንዲሁም ወንዶች ደግሞ ለባሕርያቸው የሚገባውን ሴቶችን መገናኘት ትተው እርስ በርሳቸው በፍትወታቸው ተቃጠሉ፤ ወንዶችም በወንዶች ነውር አድርገው በስሕተታቸው የሚገባውን ብድራት በራሳቸው ተቀበሉ።
28
እግዚአብሔርን ለማወቅ ባልወደዱት መጠን እግዚአብሔር የማይገባውን ያደርጉ ዘንድ ለማይረባ አእምሮ አሳልፎ ሰጣቸው፤
ስለዚህ ከፈጣሪም አኳያ ሀጣአት ውጤት መሆኑን ማሳወቅ ይገባናል ነገር ግን የዚህ አጀንዳ አሳሳቢነት የቆየ ጉዳይ ቢሆንም ከመቅረት ማርፈድ ይሻላል እንደሚባለው አሁን መነሳቱም በራሱ እውነተኛውን አመጣጡን ከእግዚአብሄር በቅጣት የመጣ መሆኑን በማሳወቅ በትውልድ ላይ ለውጥ ሊያመጣ ይችላልና በጣም የሚገርመው ነገር የግብረሰዶማዊያነት ችግር የአገራችን ተደርጎ ስለማይወሰድ በሚዲያዎችም ሆነ በሀይማኖት ተቋማት አይነሳም ነበር አሁን ግን ያ ጊዜ አለፈና እግዚአብሄር ትውልድ እንዳይጠፋበት ስለፈለገ ያነቃን ዘመን ይመስለኛል ለማንኛውም ይህንን አሰቃቂ የሀጢአት ውጤት ማሳወቅ በመጀመራችሁ ጌታ ኢየሱስ ይባርካችሁ ወላጆችም ነቃ እንበል ማንም አይታመንምና ዓይኖቻችንን ጆሮዎቻችንን ጌዜአችንን በልጆቻችን ዙሪያ እናድርግ እናሳውቃቸው እላለሁ ወላጆች የልጆቻቸውን ሞባይል ከፈት ሲያደርጉ ፖርኖግራፊ ተጭኖ የሚያገኙበትና ወሲብ መመልከትና ከጋበቻ በፊት መፈጸም የተለመደና የማይገርም ጉዳይ እየሆነ የመጣበት ዘመን ስለሆነ ከእግዚአብሄር የተሰጡን ስጦታዎች እንደቀልድ ወደ ሲኦል እንዳያዘግሙ እንጠንቀቅ
Amelake kabezi meate yesewerena.
ReplyDeleteSo sorry! This has been expected from a cursed generation. Ok, it may help some how to know to what extent the problem is intoxicating us. But I hardly believe to discuss this kind of issue on public media brings solution. perhaps there might be a back fire effect. Instead, it should better be studied by special group and design strategies to halt this damage.
ReplyDeleteWhy this is happening? Don't be as such surprised. We have become most cursed ones! Please please do not at all connect this kind of issue with culture. I know no culture in this world promoting this curse. But now a day almost all the world has already been contaminated by this. The issue is not as simple as culture. Why we Ethiopians always confuse things with culture! The issue totally is inherent deviance from nature! This after all does not exist even in animals! This is a problem of the animal that thinks itself superior (human being). 'Egziabiherin lemawek balfelegut meten yemayigebawun yadergu zend lemayireba aemiro asalifo setachew'. Very sorry! What is happening is exactly this! Ketiqitoch besteqer egziabiher endale anaminim! anaminim!!! Gimashochachin bekihidet, lelochachin begimash bicha eninoralen. Ene gehanem, genet, seol mengiste semayat lebizuwochaghin teret teretoch nachew!
Gudayun yaqerebut enatim betam yascheneqachew bahiluna mahiberawi chigiru enji meseretawiw yenefs guday aydelem! The culture and the social norms can simply change! If we are trying to control the problem with these norms we can hardly be successful. Look, how the other particularly so called developed world slowly accepted this curse! Almost so called christian leaders also accepted as normal! Look where we are moving!!! It is exactly what devil is doing. The problem is we also don't believe the existence of our enemy devil! I understand some of you who are reading my comment here may laugh when I say there devil inside! It is solid true!!! devil is there!!!!
Today many Ethiopians are learning about the power of God and the secretes of devil. Thanks to one father who unveiled centuries years old hidden realities. I don't what to mention his name but I know most of you know him! But you still are playing game! I hope this mother also know who I am talking about. She should take her son to him. He will cast off this evil spirit from her son. She should also always kneed down for God and raise here hands towards Him! That where the power can be gained! akafan akafa domanim doma belu! yihe yetedibesebese nuruachin new chigir eyefeter yalew. Sint ergimanochin eyamokashen yenorin lijochachin endih behonu lemin endenegitalen. Egziabiherin bekenferin betiqs enji meche bewunet amelekiniw! Seitanin gin bedenb new yeminigebirew! Betemeqdesochachin saiqeru yeseitan siran yemiseru yemiqedisubachew honewal. Leyam lezemenat! Gudachin sigelet bizu new! Yegna qidisina sanitay bicha new! Ergimanachinin asqediment enawuta! keziay kifuwn hulu yemaqom hail yinorenal! Beqa yih ergiman new! psychologist, psychiatrist, hakim yemiyaqomut guday aydelem! Wuyiyit yeminilew were manafesim chiras liyabisew yichilal.
Leul amlak lemayireba aemiro asalifo endayseten abiziten entseliy!! Amlak hoy newurachinin aswegid! kemayireba aemiro sewuren! Amen
Dear discussants,
ReplyDeletePlease also know that this kind of curse might be on purpose sponsored one. There are millionaires who are funding to demolish our being! Even governments are forcing all the world to join their curse! This needs critical investigation by the national security as well. Yet I fear it might soon or already intoxicated our national security. Very dangers!! They don't care but if they have ear to listen the people it is time for religious (specifically the Muslim and the old churches) people in particular to play a role. Yet, I suspect so called religions (new ones) that might be involved in promotion of this curse! Firstly there are some who on purpose are working towards demolishing the Ethiopian religious, social and cultural values and want to impose the western curses.
Dn. Dany, yhin guday masawekih betam tiru new... yemisemaw neger yasferal, yasazinalim! Baletarikua enat beketita leloch yelijachew guadegnoch beteseboch endiyawku adrgew yihon??? Esachew lijachewin sileteketatelu liyawku chalu lelochus....
ReplyDeleteD/n Daniel EGZIABHER Yibarkih; Bertalen.
ReplyDeleteአቤቱ አምላክ ሆይ ይሄን ዘር አቋርጠው!
ReplyDeleteከመዝገብ ሰርዘው ከምድ ገጽ አጥፋው !
በርኩሰት በነውር ፍጡርህ አይበከል!
እርግማኑ ይብቃ አዲስ ትውልድ ይብቀል!!!
The Bible speaks of spirits that cause physical health problems such as the spirit of infirmity, blindness, deafness, etc. along with spirits that cause fear and depression (King Saul), mental illness,HOMESEXUALITY etc.Demon bondage can be brought about when an individual is possessed, oppressed, or is in rebellion towards God (sins of the flesh). It takes God's discernment to determine which of these is producing the bondage in an individual's life.
ReplyDeleteThe Bible makes it clear that there are demons, or evil spirits, in the world that interfere in people's lives SEX or ‘Making Love,’
is the complete intimate connection
between man and woman, where they
both feel an inseparable ability to stay
together because of the ‘soul ties’ that
they have formed through their sexual
union.ኦሪት ዘፍጥረት2;24 ስለዚህ ሰው አባቱንና እናቱን ይተዋል፥ በሚስቱም ይጣበቃል፤ ሁለቱም አንድ ሥጋ ይሆናሉ።SO,HOW CAN THEY BECOME @ONE FLESH=DURING SEXUAL INTERCOURCE!A soul tie is a strong bond
formed between two people through
sex that forms the realm of their
spirit. The stronger the bond or soul
tie, the deeper and more powerful the
relationship.God had originally made
the sexual union to be the whole being
to whole being….spirit to spirit, soul
to soul, and body to body.
Sexual involvement 0(SUCH AS HOME SEXUAL ጥቃት ወይም መደፈር መንፈሱን ከመንፈሱ ወይም ከተደፈረው ልጅ ጋር ይጣበቃል ስለዚህም ልጆቹ ከዚያ በሁዋላ ወደ ተለመደው ሂዎት መመለስ የሚከብአቼው)0 can form such
entangling tentacles of soul ties that
it is extremely difficult to break off
a relationship, even an unhealthy,
abusive relationship. ..
....Normal heterosexual activity outside of marriage, which the Bible terms " ዝሙት" is already a
ReplyDeletemajor channel for demonic spirits to travel between the two parties. ሰው ከመጀመሪያው ወዳጁ ጋር ግንኙነት ካረገ በሁዋላ ግማሽ አካሉ ከወዳጁ ጋር አንድ ስለሆነ ከዚያ በሁዋላ በሚደረግ ግንኙነት እንደመጀመሪያው እርካታን አያገኝም ምክንያቱም SPRITUALBOND ስለተፈጠረ ነውThis is what we call an "ungodly soul tie." Every evil spirit that Party One possesses will travel through to the other Party as the two become one flesh in a manner that the Creator only intended to occur in marriage! - ስለዚህም አንድ ህጻን ሲደፈር በዳፋሪው ውስጥ ያሉት መናፍስት ሁሉ ወደ ልጁ ይተላለፋሉ ማለት ነው ከዚያ በሁዋላ ምንም ያህል ጥረት ቢያደርግ ከመንፈሱ እስኪላቀቅ ድረስ ከHOMOSEXUALITY ነጻ መሆን አይችልም -most sodomites are either survivors of very dysfunctional childhoods or else child sexual abuse!!!......
Homosexuality is a Distruction ....The world is almost to fight againist this....God is with Us.
ReplyDeleteEverything that we see in the earth is a reflection of something that exists in the spiritual realm!ብታምኑም ባታምኑም ግን homosexuality is AN EVIL spirit!God established boundaries around sex to protect it and maximize its joy....Sodomy was a key part of the ancient mystery religions and
ReplyDeleteseemed to have been part of the practice of the pagans surrounding Israel (remember Sodom!).
Many times, it was believed that the priests of such cults had to be in touch with their
"feminine" side. This was often achieved through bisexuality or sodomy. Often, these
priests would dress as women as well. This may well be the ancient and forgotten origin of
the "priests in skirts" act seen in the Roman church.Many of these pagan gods were androgynous (both male and female). An example is Baphomet, with the sexual characteristics of both a man and a woman.
የተዋጣለት ጽሁፍ በተለይም ስነምግባርን፣ ባህልን፣ ማህበረሰብን፣ ሃይማኖትን፣ ስነ ልቦናን/ባህርይን፣ የሃገርን ድንበር ያጣቀሰ በመሆኑ አድንቄዋለሁ፡፡ ግዜውንም የጠበቀ ነው ለማለት ግን አልችልም ምክንያቱም ተሸክመነው የኖርነው፣ ገመና ሆኖ የቆየ ይመስለኛል፡፡ ለዚህም የራሴን ልምድ ላካፍል ወደድኩ፡፡ አንዳንዶች ምንም አንኳን ከዘመናዊነት/ከስልጣኔ ጋር ቢያያይዙትም መልኩን ቀይሮ ነው እንጂ ከውጭ የወረስነው ባህል ነው ለማለት ያዳግታል፡፡ ሰሞኑን በአሜሪካ የተደረገው ‹ፍናፍንታዊነትን› በህግ የመደገፍ ሁኔታ ተከትሎ በርካታ ውጭ ሃገር የሚኖሩ የፌስቡክ ወዳጆቼ ስለ እኩልነት የሚሰብኩትን በማየት ‹እንዴ- እከሌም እንዲህ ነበር እንዴ፣ እከሊትም እንዲህ ነበረች እንዴ› እያልኩ ስገረም ነበር፡፡
ReplyDeleteበቅርቡ ያጋጠመኝ- ትምህርት ቤቱ የሚረዳው ስዊድን ሃገር በሚገኝ ግብረ ሰናይ ድርጅት ነው፡፡ ላለፉት 30 ዓመታት ምንም ዓይነት የመንግስት ድጋፍ አልነበረውም፡፡ ለበርካታ ዓመታት ሲረዳው የነበረው ይኸው ድርጅት ከዚህ ቡሃላ የምንረዳችሁ ‹ፍናፍንታዊነትን› ከደገፋችሁ ብቻ ነው፡፡ ትምህርት ቤቱም ቁርጠኛ ስለነበር የቀረው ይቀራል አንጂ… ብሎ የቀረው ቀርቷል፡፡
GUDAY HULETs
ReplyDeleteበእውነቱ ከሆነ ዲ/ን ዳንኤል በማናቸውም ማህበራዊ ጉዳዮቻችን የምታነሳቸው ኃሳቦች በሀገሪቱ ታላላቅ ተቋማት እና ሲያነሱት የማንሰማቸውን እጅግ አሳሳቢ እና ትኩረት ልንሰጥባቸው እንድንችል በአይነ ህሊናችን ልንቃኘው የሚገባንን ነው፡፡ ይህ ጉዳይ ግን እንግዳ ከሆነባቸው ኢትዮጵውያን አባቶች መካከል አንዱ ነኝ፡፡ እንደተባለውም የነጮች ችግር እንጂ የእኛ ሊያውም የህጻናት ተማሪዎቻችን ችግር ይሆናል ብዬ ላፍታ እንኳን አስቤው አለማወቄ ሳስብ እኔን መሳዮቹም ሆን ሌሎቻችን ለጉዳዩ ትኩረት ሰጥተን ወደ መፍትሄ ልንሄድ እንድንፋጠን አደራ እላለሁ፡፡ ሁላችንም በየኃይማኖትና በየማህበራዊ ተቋማቶቻችን ስንሰባሰብ ጉዳዩ ልዩ ትኩረትን እንዲሻ ተገንዝበን ለመንግስት ግብዓት የሚሆኑ የመፍትሄ አቅጣጫዎችን እንድንጠቁም አሳስባለሁ፡፡
ReplyDeleteዲያቆን ዳንኤል እጅግ አሳሳቢ ስለሆነው ጉዳይ ስለጻፍህ ደስ ብሎኛል፡፡ ይህን ጉዳይ በተመለከተ ከዛሚ 90.7 ራዲዮ ኢትዮፒካሊንክ ፕሮገራም አሳዛኝ ዜና ከሰማሁ በኋላ የተሰማኝን ስሜት ከተብሁ (ጦማሩን www.geezbet.com ላይ ማንበብ ይቻላል)፡፡ ከቀናት በኋላ ያንተን ጽሁፍ ሳነብ ደግሞ ምን ማድረግ እንዳለብን ግራ ነው የገባኝ፡፡ ብቸኛ መፍትሔው ትውልድን ማንቃት ይመስለኛል፡፡ ትውልድ እንዴት ይነቃል የሚለው ደግሞ ሌላ ጥያቄ ነው፡፡ የመገናኛ ብዙኃን እንቶ ፈንቶ ከማውራት ሕብረተሰቡን ቢያነቁ መልካም ነበር፣ ግን ለዚህ የታደልን አይደለነም፡፡ ብዙ ወላጆችም ልጆቻቸውን አያውቁም፡፡ ይህ ደግሞ ሌላ ራስ ምታት ነው፡፡ ለማነኛውም ስለዚህ ጉዳይ አገራዊ አጄንዳ አድርጎ ለመወያየት፣ መፍትሔ ለማምጣትና ህብረተሰቡን ለማንቃት አክቲቪስቶች ቢነሱ ጥሩ ይመሰለኛል፡፡ የሃይማኖት ተቋማትም ከፍተኛውን ስራ መስራት እንዳለባቸው አምናለሁ፡፡
ReplyDeleteBESMAB WEWELLED WEMNFES KEDUSS AHADU AMLKE.
ReplyDeletemy job includs transtaltion and interpretation
ReplyDeleteonce we were called for one day training and we were given how to interpret for lesbian and gay people with out touching their feeling.that was the direct message but indirectly they were trying to tell us being gay and lesbian can be innate and we have to respect their right as humans they even try to make us feel sorry for them by showing us films that shows there society being attacked.World is going mad it is our duty to protect our society.Our people has to know not everything that the westerns did is civilization.Civilization is knowing our roots and respect ourselves.
This page is filled with hate and prejudice. Does anyone in this conversation have love in them? Why all the hate? I know you people think you are the cleanest people on earth without any sin. Calling gays sick people is disgusting. They are human like you and me, and they should be treated like such. I know most of the people in this page don't have any scientific understanding of anything. You base your entire argument on the moral code of a book written some 3000 years ago by uneducated sheep herders and farmers somewhere in the middle east. Let me explain homosexuality in modern terms. Most of the time a person doesn't just become gay. Can any of you tell me the day you decided you will love only women.Gays are born that way. the evidence is in the DNA. Now there is something called gay gene. (again I know you don't believe in science) You believe in science only when it fits your understanding. The other thing I hear in this conversation a lot is gays rape young boys. The fact is most rape of boys in the world happen by men who are heterosexuals(men who love woman). There was one study that came few weeks ago that shocked me. This study showed, Pakistan and Kenya as the biggest gay porn viewers in the world through the internet. But both these countries are also the most homophobic toward gays (they hate gays). There is also one study I think is also important to mention, which says people who hate homosexuals vehemently, turn out be gays themselves, and they hate gays because of self-hate(they hate the fact that they have sexual attraction of other males). Every society has homosexuals in it. It is a fact. You can't do anything about it. And what surprise me the most about this subject is why do you care about someone's business. If two men or women love each other, why would you want to stop them? They can do anything they want in their bedroom. If they love each other, who are you to say your love is less important than mine. If your religion is teaching you to judge and hate others, that is not a religion worth following. Most of you here are from an old generation.You are extremists and religious fundamentalist. you will die out and other generation will replace you. I know in my heart that the young children who are growing up to be adults will be more tolerant, accepting, and loving than you. You are just the remnants of the old days. Our generation will be one that follows reason and science, NOT dogma.
ReplyDeleteGays are born that way. the evidence is in the DNA. Now there is something called gay gene. (again I know you don't believe in science) ...A team of international researchers has completed a study that suggests we will probably never find a ‘gay gene.' Sexual orientation is not about genetics, say the researchers, it's about epigenetics. This is the process where DNA expression is influenced by any number of external factors in the environment. And in the case of homosexuality, the researchers argue, the environment is the womb itself.http://io9.com/5967426/scientists-confirm-that-homosexuality-is-not-genetic--but-it-arises-in-the-womb አዎ ወዳጄ የጌይ GENE አለ የሚለውን ሳይንሱን እኔም አልቀብለውም ይልቅስ ፍቅር እንጂ ጥላቻ አንስጥ የሚለውን ተቀብያለሁ አዎ በግልጥ ስለችግሩ መወያየት አለብን እኔ ምናልባት አንድ ከልብ የምመክርህ...መምህር ግርማ ወንድሙን ካወቃቸው እሳቼው ጋር ሂደህ እንድትፈወስ ካልፈወሱህ አንድ ለ አንድ ተወስንህ መኖር ትችላለህ ግን እርግጠኛ ሁኔ ነው የምነግርህ ብዙ ጌዮች እሳቼው ጋር ሂደው ተፈውሰዋል ይህን ስልህ ከ ልቤ ነው
DeleteFirst of all biology as a science is the most infant one though it is almost with an age of human history. Yet, science it (which ever) has never said things area all reasoned out. please the above writer imagine the universe. how much par to the universe is known in science. Don't also think that the discussants here are dogmatic. If we get reason for what is happening ok that is good. But there are oceans of realities but can little be justified. There still are in science that have no concrete evidences but only postulated. Biology in particular is full of postulates and theories. Sequencing the the entire human genome could not bring the solution that had been expected. Secretes are still intact as they had been earlier. No one here say they are not human being. After all neither of us can protrude our thong on to them. The reality is as what is mentioned by your commenter above. Most of our behaviors are influenced by external factors. Sexual feeling is one which critically is affected by environment. The inherent biology is only a seed. Being a gay is ofcourse environmentally driven. One day a normal person might be a gay. Our mind is changes due to what we see what we hear, what we exercise. This is happening. No the generation is not as you said reason oriented. We (this generation) after all are not a critical thinker. Better thoughts were in earlier times. These days believe or not are most confused. Don't think that the current technology is the result of this generation. This generation has become so soft and very loss, wild, behaving below animal. The old thoughts ofcourse were not from the blue. The bible is right. You may say dogmatic. But we can't escape from realities. The devil is there. For you who believe in science devil might not in existence. The reality are not what we know but realities are the realities themselves. God is there to safe guard us! That is true. Alemamenachin yeegziabiherin hiliwuna ayasqerewum. Hulachinim kesu beraqin qutir yemigetimen adega new enji. Ene nitsuh negn yale ezih yale aymeslegnim. Ewunetaw awo ergiman new!!! DNA has nothing to do with our such bobish behavior. Limimidachinina egziabiherin lalemaweq yehedinibachew mengedoch hulu lezih ergiman abiqitewunal. Let's really be critical! Science has never explored the ultimate realities. That is why we always are researching! There are little conclusions in science!
DeleteAgain please know that some of us are scientists specific in area you are talking about. One day when you learn the secrete you come down. Explore the secret of spirit. Those in flesh are very easy. Yimenfesin mistir sinawuq ewuqtachin hulu bado endhone eniredalen. Kefelegih mawek tichilaleh. sewoch zim bilew eyaweru aymselih. Yehaymanote neger teret teret silehonebin new ewunetin lemredat endih aqim atiten yeteshmedemediniw. Biology would have had better progress if the spiritual world had been under considerations.
Deleteእንግባባ ወገን ወዴት ወዴት እየሄድን ነው? የረሳሀቸው ሦስት ዋና ዋና ነጥቦችን እንጠቁምህ::
Delete1)ሳይንስና እምነት ምንና ምን ናቸው?
ዋናው ነጥብ መጽሐፍ ቅዱስ ከእረኝነት በተጠሩ የዓለም ምናምንቴዎች መጻፉና ሳይንስ በሚራቀቁ የምርምር ሰዎች በየዘመኑ የሚዘምን ተለዋዋጭ መሆን አይደለም:: ሳይንስ እየፈረሰ የሚሰራ መሆኑ የእውነታው ማሳያ ተደርጎ ሊወሰድም አይችልም:: እምነትም ዘመን ማስቆጠሩ እንደዚያው:: የክርክሩ ነጥብ ያለው እምነት የሚያምነው የተገለጠ ነው:: በዚህ ምክንያት ዐለት ነው:: ሳይንስ እንደ ጭቃ የሚቦካ ተለዋዋጭ ነው:: ሳይንስ በጠባዩ ወደ እውነት ሲደርስ የእምነት ምስክር ነው የሚሆነው:: እምነት ለሳይንስ መነሻም መድረሻም መሆን ይችላል:: ሳይንስ የእምነት መነሻም መደምደሚያም መሆን አይችልም:: የማይዛመዱ ነገሮችን በግድ ልናዛምዳቸው አንችልም:: ስለዚህ በሳይንስ የምታስረዳን ከሆነ ቤተ እንነቱን ከወቀሳ ተወውና በሳይንስ እንነጋገር::
እውነት አንተ እንዳልከው የግብረ ሰዶማዊነት ተፈጥሮአዊነት በሳይንስ የተረጋገጠ ነው? ድጋፍስ አለው? እውነት የምታወራ ከሆነ ጥቀስ ጠቅሰን እንንገርህ:: ነገር ግን አትሳሳት ጥቂት ሰዎች ያውም በችግሩ ውስጥ ያሉ ሰዎች ተናገሩ ብለህ ሳይንሱንም ባታሳጣው መልካም ነው:: ሌውን ሁሉ ትተነው ሳይንስ ከተፈጥሮ ጋር ሲስማማ እንጂ ሲቃረን ቅቡል አለ መሆኑን ማወቅ አለብህ:: እምነት ከተፈጥሮ ጋር አይጣላም:: ይልቁንም እምነት የሚተጋው ሰው ተፈጥሮአዊ ክብሩን እንዲጠብቅ ነው:: ምሳሌ ዘር ስለ መቀበል ምን ትላለህ? ሴት ልጅ ዘር ልትቀበል ተፈጥሮ አዘጋጅቷታል:: ሌላ ጾታ አይደለም ራሷ ሴቲቱ የምታደርገው ተራክቦ ከተፈጥሮ ፈቀቅ ሲል ምን ይከሰታል? ጤናማ ያልሆነ እርግዝና ከሚፈጠርባቸው ምክንያቶች መካከል ይሄ አዱ ምክንያት መሆኑን የሕክምና ባለ ሙያዎችን ጠይቅ::
2)ስለ መዋደድ ፍቅርና መከባበር የምንሰብከው ከሕገወጥነት ጋር እንዴት ይታያል?
የፍቅር ጥግ ምሳሌውን ከአምላክ ተምረን ከሆነ በከሀዲው ሰይጣንና በተሳሳተው አዳም ላይ የወሰደው እርምጃ የቱን ይናገራል ጭካኔውን ወይስ ፍትሐዊነቱን? ግብረሰዶማዊነትን የዝሙት አዳሪነት ያህል ልንታገሰው አንችልም:: ለሕሙማኑ የሚኖረን ርሕራሄና ለድርጊቱ ያለን ጥላቻ የሚወዳደር አይደለም:: በሕጋችን ወንጀል በእምነታችን ኃጢአት በባሕላችን ነውር ነው ብለን ተስማምተናል:: ከዚህ አልፎ ለሚሄድ ሁሉ የርህራሄ ልብ የለንም:: ሊኖረንም አይችልም:: ከዚህ በኋላ ያለው ነገር የፍትሕ ጥያቄ ነው የሚሆነው:: ፍትሕ ፍቅር ነው ፍቅርም ፍትሕ ነው:: ለተደፈሩና ለሚደፍሩ እኩል ሚዛን እንዲኖረን የምትሻ ከሆነ የዓለም ቁጥር አንድ የዋሁ አንተ መሆን አለብህ:: የሚዲያዎቻቸው ልቅነት የፈጠረውን ሕገ ወጥነት የማስታመም ግዴታ የለብንም:: ራሳችንንና ቤተሰባችንን እንጠብቃለን:: ሕገ ወጦችን በፍትሕ አደባባይ እናቆ ማለን::
3)ሥልጣኔ ምንድንነው?
የሰውን መብት ያለ ገደብ ማክበር ነው ብለው ከሚያስቡት ጋር የምትተባበር ከሆነ የሰው ልጅ ጣሪያ አልባ ፍላጎት ጎርፍ ሆኖ ይወስድሀል:: ሥልጣኔ ተፈጥሮን በተለያየ ገጽ ማንበብ መቻል ነው:: ከተፈጥሮ መማር ነው:: ለስው ልጅ ኑባሬ ገንቢ አስተዋጽኦ ማበርከት ነው:: ልቅነት አይደለም፥ ራስን መግዛት ነው:: ከሚበልጡን ሰዎች የምንማረው ከስህተታቸውም ከስኬታቸውም ሊሆን ይችላል:: የምንወስደውና የምንተገብረው ግን የሚሻሉበትንና ያለፉበትን እንጂ የወደቁበትን አይደለም:: ሰለጠኑ ካልካቸው ሳይንቲስቶች አዳዲስ ግኝቶችን ይዘህልን ና::
እንደ ማጠቃለያ የችግሩ ተጠቂ ከሆንክ በተለይ እየሄድክበት ያለውን መንገድ አጭር በጣም አጭር አድርገኽዋልና አስብበት:: የተደመደመ ሕይወት ያለው የሰው ፍጡር የለም:: መመለስና ክርስትና የሚያጎናጽፈውን ነጻነት ተቀዳጅ በቀደመ ማንነትህ ሳይሆን በመመለስህ የምናውቅህ አስቀድመህ የእረኞች ድርሰት ያልከው መጽሐፍ ካስተማረን የተነሳ ነው:: ጠባችን እንደ አበደ ውሻ አድብተው ሕጻናትን ከሚነጥቁን ጋር እንጂ የችግሩ ተጠቂዎችንማ ልናክም ልንንከባከብ ግዴታ አለብን::
Daniel, You have to try to understand these thought. please Read it again and again. May The "God" open your mind!
Deleteሰዶማዊያን የተፈጥሮን ሥርዓት አፍርሰው ከተፈጥሮ ውጭ በሆነ መንገድ ሊረኩ የሚሞክሩ ናቸው:: አንዳንዶች እርስ በእርስ ሴጋና /ራስን በራስ ለማርካት ጥረት ማድረግ/ በፊንጢጣ “ወሲብ” ስለማይረኩ ካሮት፣ ጠርሙስ፣ ባትሪ . . . በፊንጢጣ በኩል በመክተታቸው ከተፈጠረው ጭንቀት ለመዳን ወደ ሆስፒታል ይመጣሉ:: ፊንጢጣን ከመላስ ባሻገር በተግባር ሠገራ ይበላሉ:: ከዚህ የተነሳ በተለያዩ የበሽታ ዓይነቶች ይጠቃሉ:: ራሳቸውንና ዓለማችንንም ለበርካታ ማኅበራዊ ቀውሶች ይዳርጋሉ:: ይህ ሁሉ የሚያመለክተን ከተፈጥሮ ውጭ በሆነ ፍትወትና ሴሰኝነት ታስረው ለማይገባ ነገር ባሪያዎች ሆነው መገዛታቸውን ነው:: ለዚህ ነው በአንዳንድ አገራት ግብረ ሰዶማዊነት እንደ በሽታና የአእምሮ መዛባት የተመዘገበው:: ይሁን እንጂ ደግሞ ሰለጠኑ የሚባልላቸው አንዳንድ አገራት ይህን የመሰለ አጸያፊ ድርጊት: እንደ መብትና የነጻ አስተሳሰብ መገለጫ ይቆጥሩታል:: ከዚያም አልፈው ለአፍሪካውያን መብትና ሕይወት ተቆርቋሪ በመምሰል እንደ ሸቀጦቻቸው ሁሉ የነውረኛ ድርጊታቸውም ማራገፊያ ሊያደርጉን ይከጅላሉ:: ግብረ ሰዶማዊነት ስሜቱን የሚያረካበት፣ ምኞቱን የሚገታበት፣ በቃኝ ብሎ የሚቆምበት፣ ነውሩን የሚሸፍንበት ጣሪያ የለውም:: ማናችንም ማወቅ ያለብን ዋነኛ ጉዳይ ግብረ ሰዶማዊነት የርኩሳን መናፍስት /የአጋንንት/ የጥፋት ሴራ መሆኑን ነው::
DeleteI agree with the fact that we all are sinners, true! why judge? Yes we are not in a position to judge! However, I believe human beings are the most talented, self organized and civilized animal, so why human do what is against nature in which no other animal do? You say there is love, if really there is love between why have too many affairs? and one more thing my beloved modern person, just few days ago NASA scientist has found two tablets with the ten commandments and they say God is real and Christianity is the one true religion (in which is based on the bible written by did you call them herders?). They did not wrote it, it is God's real words believe it or not. Another issue with respect to your scientific evidence if you really read about science do you know the food that we eat today (GMO) has the ability to destruct many of our nature especially gender related issues infertility, early detection of period in girls, more estrogen hormone in males (which makes you act like a girl while you are boy), and many more abnormalities? I say may God forgive us all, May we see his love so that we worship and love him with all our hearts, May we obey him the way he wanted us! I say you would have been more worried about this issue if you have kids but then such people are not lucky enough to see the love of children than lust.
DeleteDn Dani may God bless you more and more, may Christ bless your kids and family!
What did you say there is a Gay Gene ? there is only Gay Gini, if there were a gay DNA it has to be inherited from family right ? so how is that a boy or Girl from a Heterosexual family could inherit a Gay Gene? from whom ? You put science as a justification here, that is bullshit science is too child to understand Humanity.
DeleteThe only goal of Homosexuality is a sponsored Extinction of Humanity on this Earth then to change How Humans breed to Glass Tubes. Then to stop Mother and Father relationship where the Humans will become Robots.
Accepting Gays in ones society doesn't go with Individual freedom at all it is Like planting a time bomb of Extermination for that society.
I wonder may be you are from The Gay Nations like USA, France and so on.
ሰይጣን ተለቅቋል፣ ከሁሉም አቅጣጫ ዲያብሎሳዊ ጦርነቱን ከፍቶብናል። ጦርነቱ በቅድሚያ መንፈሣዊ ባሕርይ አለው፤ የሚጓዝበት መንግድ ግን ደካማውን ሥጋዊ ማንነታችንን እየተገለገለ ነው። ሥጋዊ / ቁሳቁሳዊ ድህነታችን ዋናውና ውዱን ኃብታችንን : መንፈሣዊ እኛነታችንን እየተፈታተነ ያቃውስብናል።
Deleteየሕብረተሰባችን ዋና ምሰሶዎች የሆኑት ሕፃናቶቻችንና ሴቶቻችን ለዚህ ዲያብሎሳዊ ጥቃት በቅድሚያ እየተጋለጡ እንደሆነ አሁን የምናየው ነው። ለመንፈሳዊ ሕይወታችን ጤንነት እናቶቻችን፣ እህቶቻችን፣ ሴት ልጆቻችን እና ሚስቶቻችን በጣም ከፍተኛ የሆነ ሚና ይጫወታሉ። የመጨረሻዎቹ ቀናት ላይ እንገኛለን። ብዙ የታሪክ ዘመናትን ያሳለፍን፣ ተወዳዳሪ የሌለውን የስቃይ ፈተና ያየን እኛ ኢትዮጵያውያን እስከ መጨረሻው ልንዘልቅ ጥቂት ነው የቀረን። Child molestation and pedophilia (sex with children) occur far more commonly among homosexuals than among heterosexuals on a per-capita basis, according to a new study. In her thesis – also written for the Regent University Law Review – Doctor Judith Reisman cited psychologist Eugene Abel, whose research found that homosexuals “sexually molest young boys with an incidence that is occurring from five times greater than the molestation of girls. …”
Gay press promotes sex with children
When lost men and women reject the Lord Jesus and His salvation they open themselves to accept all kinds of sins from the devil. People who reject God always grow close to Satan and accept his ways.
Here is what will happen in regard to Satan’s prospering of the sin of sodomy:
- It will increase in media exposure. Expect more TV shows and movies to glorify this sin
- Of course rock and rollers will continue to promote this sin since many of them are already sodomites.
- At first many people will be upset at seeing all the pro-sodomite TV shows and movies
- Over time, due to exposure, they will become de-sensitized to the sin of sodomy. It will no longer be seen as a repulsive act.
- After people are de-sensitized they will begin to view the TV shows and movies and find them interesting or entertaining
- After more exposure some people will begin to show an interest in the sodomite lifestyle
- The final step in this downward process will be more people trying and experimenting with sodomite sex. Some will become practicing sodomites while others will consider themselves bi-sexual.
- Of course through it all sexually transmitted diseases will increase in the general population who do these immoral acts.
The goal of the Homosexual Agenda is no less that making it their civil right to allow homosexuals to have sex with our children... a pedophile justifies having sex with children because he/she has convinced their selves that they are not hurting the child; rather they believe they are loving the child.የጥንታውያን ሰዎች አጥንት እንፈልጋልን ብለው ወደ ኢትዮጵያ የመጡት አሜሪካዊ የአርኪዎሎጂ ሊቅ፣ ዶናልድስ ዮሐንሰን፡ ታዋቂዋን “ሉሲ” ሉሲ የሚለውን ስም የሰጧት፡ አጽሞቿን ባገኙበት ወቅት የእንግሊዛዊውን የሙዚቃ ቡድን፣ የ ‘ቢትልስን” ዘፈን “Lucy in the Sky With Diamonds” እያዳመጡ ስለነበር ገልጠውልናል። ግን ይህ እውነት ነውን? ሉሲ የሚለው ቃል “Luce” ከሚለው የላቲን ቃል የመነጨ ሲሆን፡ ትርጉሙም “ብርሃን” ማለት ነው። Lucifer ብርሃኑ ክርስቶስ ሳይሆን እኔ ነኝ ይላል። እግዚአብሔር ግን እንዲህ ይለዋል፡
“አንተ የንጋት ልጅ አጥቢያ ኮከብ ሆይ፥ እንዴት ከሰማይ ወደቅህ! አሕዛብንም ያዋረድህ አንተ ሆይ፥ እንዴት እስከ ምድር ድረስ ተቈረጥህ! አንተን በልብህ። ወደ ሰምይ ዐርጋለሁ፥ ዙፋኔንም ከእግዚአብሔር ከዋክብት በላይ ከፍ ከፍ አደርጋለሁ፥ በሰሜንም ዳርቻ በመሰብሰቢያ ተራራ ላይ እቀመጣለሁ፤ ከዳመናዎች ከፍታ በላይ ዐርጋለሁ፥ በልዑልም እመሰላለሁ አልህ።
ነገር ግን ወደ ሲኦል ወደ ጕድጓዱም ጥልቅ ትወርዳለህ። የሚያዩህ ይመለከቱሃልና። በውኑ ምድርን ያንቀጠቀጠ፥ መንግሥታትንም ያናወጠ፥ ዓለሙን ሁሉ ባድማ ያደረገ፥ ከተሞችንም ያፈረሰ ምርከኞቹንም ወደ ቤታቸው ያልሰደደ ሰው ይህ ነውን? ብለው ያስተውሉሃል።” [ትንቢተ ኢሳያስ 14፥12-17]
ስለዚህ ህጻናቶቻችንን፣ ሴቶቻችን ከነጣቂው ሉሲፈር ከነፍሰ-በላው አውሬ ነቅተን ጠንክረን ልንጠብቅ ይገባናል፡ ለዚህም ኢትዮጵያኛው እምነታችን ጦራችን፡ ፍቅር ደግሞ ጋሻችን ናቸው።
Will the Orthodox Church do same-sex marriages?
DeleteNo, we won't.
Let me explain why. Marriage has always been between males and females. That is the very meaning of the word. Some cultures in history, most famously ancient Greece, were -- shall we say -- rather easygoing about homosexuality. But even they never accepted same-sex marriage as an open and legal institution.
If this huge change now takes place, as it seems it might, it will be a first in the history of the human race. Marriage is one of the holy sacraments of the church. And it has always been between a woman and a man. To change this would be to change the very nature of the sacrament and that we cannot do.
The sacrament of Christian marriage reflects the loving union between Jesus Christ and his church. This is clear in the epistle lesson written by the Holy Apostle Paul, Ephesians 5:21-33, which is read at every Orthodox wedding. In this epistle reading, St. Paul clearly teaches that the marital union reflects the union between Christ, the bridegroom, and his spouse the church, the bride.
A human bride and groom hopefully have a similarly loving relationship and union as do Christ and his church. But the marriage between Christ and the church can't work if there are two Christs and no church, or two churches and no Christ! And, similarly, the human marital reflection of the union between Christ and the church won't work if there are two human brides and no groom, or two grooms and no bride.
To have such a "marriage" would make nonsense of everything Paul says and that fact shows that such a "marriage" really isn't marriage, no matter what terminology we humans wish to use. Ultimately, real marriage is what God says real marriage is, not what we say it is. Through the inspiration of Scripture by the Holy Spirit, God has spoken through the writings of St. Paul.
Both the Bible and the tradition of the church teach that same-sex sexual activity is sinful. It's not an unforgivable sin or the worst sin, but it is a sin. Therefore, the church asks those who are tempted to such sin to refrain from it and be chaste. In a similar way the church asks those with no same-sex struggles to refrain from heterosexual sexual activity outside of marriage. Chastity is asked from both and it is believed that God can help a person remain chaste.
So in closing, the Orthodox Church is happy to minister to those struggling with homosexuality. Such ministering goes on pretty much everywhere and in most parishes --our people have the same struggles as everyone else does. We certainly have no hatred against people with this struggle and no interest in "gay bashing."
We will not turn someone away because of a particular sin they struggle with. They are sinners like the rest of us who need God's forgiveness and help.
But performing or approving of same-sex marriages? No, we can't do that. That would be saying that what is a sin isn't a sin. That would be a lie, so we can't participate or approve.
May God have mercy on all of us sinners and bring us to repent of our sins and bring us all into his heavenly kingdom.
ወላጆች ስለፌስቡክ እንደ ወላጅነት ሊያውቋቸው የሚገቡ ነገሮች
ReplyDeleteወላጆች ለበይነመረቡ (Internet) ዓለም በልጆቻቸው ህይወት ላይ ቁልፍ ሚና መጫወት አለባቸው፡፡ ልጆቻቸው ጥሩ የሆነ የራስ መገለጫ እንዲኖራቸው፣ ጥሩ ግኑኝነትን እንዲመሰርቱ እና የማህበራዊ ድረ ገጽን በመጠቀም ቀና የሆነ ስእብና ማትረፍ እንደሚችሉ ማሳየት ይኖርባቸዋል፡፡ ለወላጆች ይጠቅማል ከሚባሉት የማህበረሰብ ድረ ገጽ አጠቃቀም መመሪያዎች ውስጥ ጥቂት ልበል፡
• የፌስቡክ ጥቅም ፍጹም ለግል ነው፡- ለዚህም ነው የመጀመሪያው የጥንቃቄ መርህ “ከልጆችዎ ጋር ይነጋገሩ” የሚለው፡፡ ወላጆች ከልጆቻቸው ጋር ለመነጋገርት የማህበራዊ ድረ ገፅ አዋቂ ወይም ሊቅ መሆን አይጠበቅባቸውም፡፡ ለምሳሌ፡- ለምን ፌስቡክን መጠቀም እንደፈለጉ በመጠየቅ፣ የጊዜ ሰሌዳቸው ላይ ምን ምን ማካተት እንደሚችሉ እንዲያሳዩቻችሁ ማድረግ፣ የትኞችቹ አይነት መረጃዎች በማህበረሰብ ድረ ገፅ ብንለቅ/ብናካፍል ተገቢ ይሆናል ወይም ተገቢ ያልሆኑት የትኞቹ ናቸው ወ.ዘ.ተ የሚሉት ከልጆችዎ ጋር ጥሩ መነሻ መነጋገሪያ ነጥቦች ናቸው፡፡
• እንደወላጅነትዎ የመፍትሔም አካል ነዎት፡- ምንም አይነት መጥፎ ነገር ቢከሰት ሊነገርዎት ይገባል፡፡ ስለፌስቡክ ወይንም ስለሌላ የማህበረሰብ ድረ ገጽ ብቻ አይደለም በተለይ ልጆችዎ የበይነመረብ (Internet) አጠቃቀማቸው ምን እንደሚመስል፤ የእርስዎን እርዳታ ይፈልጋሉና፡፡
• ምንም ዓይነት መጥፎ ነገር ቢከሰት ላለመቆጣት ይሞክሩ፡ ለእርስዎ እንዲነገርዎ እና የመፍትሔ አካል ለመሆን እንዲችሉ ይረጋጉ! ልጆች ወደ ወላጆቻቸው ለመሄድ እና ለማማከር የሚደፍሩት ከወላጆቻቸው ጋር የሚያደርጉት ንግግር እረጋ ባለ እና አሳቢነት በተሞላበት መንፈስ እንደሆነ ይወቁ፡፡ በይበልጥ ሊረዱዋቸው የሚችሉት ልጆችዎ እርስዎን ለማናገር የመረጡ እንደሆነ ብቻ ነዉ፡፡ ስለዚህ ከእርስዎ ጋር እንዲነጋገሩና እንዲረዷቸው ያለውን እድል ያሰፋሉ፡፡
• በአሁን ጊዜ እየተለመደ የመጣውን የተጠናከረ ቤተሰባዊ መመሪያዎችን መጠቀም (The well stocked toolbox of today’s parenting)፡ በቤተሰብ ውስጥ ዋጋ የሚሰጠውን ወይንም መከበር ያለባቸውን ህጎች በደንብ ማጠናከር፤ የቤተሰብ ህግንና መመሪያ ማውጣት፤ ለምሳሌ የኢንተርኔት መጠቀሚያን በግዜ ሰሌዳ ተግባራዊ ማድረግ፡፡ አንዳንዴም የወላጆች መቆጣጠሪያ መሳሪያዎችን ወይንም ቴክኖሎጂዎችን መጠቀም፡፡ ወላጆች እነዚህን መሣሪያዎች እየተጠቀሙ ከሆነ ለልጆችዎ የመቆጣጠሪያ መሳሪያዎች እየተጠቀሙ መሆኑን መናገር እንዳለባቸው ይመከራል፡፡
• ሌሎችን ለወላጆች ጠቃሚ የሚሆኑ ምክሮችንም በ https://www.facebook.com/safety/groups/parents/ ፌስቡክ አድራሻ ታገኛላችሁ፡፡
ሁለት ሰዎች በጋብቻ ሲጣመሩ ሁለት አንድ ይሆናሉ!sex ሁለት ሰዎችን እርስ በርስ የሚያስተሳስር ከሆነ ተፈጥሩዊ ያልሆነው ግብረ ሰዶምም ሆነ ዝሙት እንዲሁ የዚያች ሰው ነፍስ አብሯት ግንኙነት ከፈጸመው ሰው ጋር ሁሉ ትተሳሰራለች1ኛቆሮንቶስ6;16 ወይስ ከጋለሞታ ጋር በዝሙት የሚተባበር አንድ ሥጋ(one soul) እንዲሆን አታውቁምን? ሁለቱ አንድ ሥጋ ይሆናሉ ተብሎአልና !! በተለይ ለመጀመሪያ ጊዜ የሚደረግ የውሲብ ጥምረትን በጣም ለመላቀቅ ይከዳል ለዚህም ነው ሄዋን እንዲህ የተባለችው ኦሪት ዘፍጥረት 3;16 ፈቃድሽም ወደ ባልሽ ይሆናል! ለዚህም ነው ሃዋርያው ጳውሎስ ሮሜ 6፥18
ReplyDelete«ከዝሙት ሽሹ። ሰው የሚያደርገው ኃጢአት ሁሉ ከሥጋ ውጭ ነው፤ ዝሙትን የሚሠራ ግን በገዛ ሥጋው ላይ ኃጢአትን ይሠራል»ያለው ይህ ማለት ዝሙት ራሱ በስጋው ላይ መንፈሳዊ ብቻ ሳይሆን ስጋዊ ጠንቅ አለው እያለን ነው...
ከእውቀት ነፃ የመሆን ችግር
ReplyDeleteአንድ ቀን ያለፈውን የመልአኩን የቅዱስ ሚካኤልን በዓል ዝክር ከቤተሰብ እና ከጓደኞቼ ዝክር ተጠርቼ ጠበል ጠዲቅ እየቀመስኩ እንዲሁ መፈታተን ፈለኩና አንድ በኣንድ የ100ብር ጥያቄ አለኝ ብዬ ‹‹ ዛሬ ሊቀ መልአኩ ምን ያደረገበት እለት ነው›› አልኳቸው፡፡ ሁሉም በማፈር መሳቅና መቀለድ ጀመሩ፣ በቀልድ አስመስሎ ሶስቱን ልጆች ከእሳት ያወጣበት ቀን ነው ያለኝም አለ፡፡
የእኔም የጥያቄ አላማ የነበረው ይሔ ነበር፣ በጣም ብዙ የኦርቶዶክስ አማኞች ስንባል የሞራል ደጋፊ ነን እንጂ ከቤተክርስቲያም ሆነ ከሃይማኖት ዕውቀት ነፃ ነን! በነገራችን ላይ ቅዱስ ሚካኤል የባህራንን የሞት ደብዳቤ ወደህይወት የቀየረበተ እለት ነበር፣ ሰኔ ሚካኤል
በሚያሳዝን ሁኔታም የሰኔ 21ን በዓል አገር ሲቀውጠው፣ ጉዘጓዝ፣ ቄጤማ፣ ዳቦ፣ ጠላ፣ ጠጅ ሁሉ ተጥሎ፣ እለቱን ሲዘክሩ ከነበሩት በተሰብም ሆነ ጓደኞቼ፣ ቅድስት ሥላሴ ያሳያችሁ አሁንም የበኣሉን ምንነት ጠይፈቄያቸው አንዳቸውም አልመለሱልኝም…( የጠሎቱ መጽሃፍ ራሱኮ የሰኔ ጎለጎታ ነው የሚለው፣ ጌታችን አንደኛ ካህን ቅዱሰድ ጴጥሮስ ሰራኤ፣ ቅዱስ እስጢፋኖስ ዲያቆን ሆነው ቅድሰው የጌታችንን እናት እመ ብዙሃንን ስጋ ወደሙን ያቀበሉበት እለት ነበር)
እኛም፣ ቤተሰቦቻችንም፣ መንግስትም ለቤተክርስቲያንና ለሃይማኖት ትምህርት፣ ስለምናመልከው አምላክ ማንነትና ምንነት፣ ስለ ቤተክርስቲያን ስርዓት፣ ስለ ዐዕማደ ምሥጢራት፣ ስለ ቅዳሴ፣ ስለ ወንጌል ትርጓሜ፣ ስለ ገድላትና ስለ ተዓምራት አንድ ጊዜ በቻ ሳይሆን ከጊዜ ወደጊዜ ከአመት አመት ምንም ቦታ የማንሰጥና የማናውቅ ከሆነ እኛስ ምን እንድሆን ልጆቻችንስ ምን እንዲሆኑ፣ የልጅ ለጆቻችንስ ምን እንዲሆኑ እንጠብቃለን ! ደናቁራን እኮነን!
ዓለምኮ ከመሬት ተነስታ እዚህ የሃጢአት ብቃት ደረጃ አልደረሰችም፣ በጣም ብዙ ደክማለች፣ እንዴት ነው እኛ ፈታ ብለንና ተዝናንተን የዚሀን አለም ፈተና የምናልፈው፡፡ መድከም ያስፈልገናል፣ የማወቅ ፍላጎት እንዲኖረን ያስፈልገናል፣ እኛም ቤተክርስቲያን ሄደን መማር ያስፈልገናል፣ የንስሃ አባቶቻችንን በጥያቄና መልስ (ማስታወሻ እያያዙ፣ እያታቀሱ፣ እያመሳከሩ፣ መፅሐፍትን እያገላበጡ) ማጨናነቅ ያስፈልገናል፣ ልጆቻችንን ቅዳሴ ይዘናቸው እንድንሄድ ያስፈልገናል ኤድና ሞልና ዘመድ ቤት ለልደትና ለምርቃት ብቻ አይደለም፣ ተሰጥኦ ስንቀበል መስማት ያስፈልጋቸዋል( በነገራችን ላይ የንስሃ አባቶቻችን ጠበል ለመርጨት ቤት ሲመጡ፣ ሰብሰብ አድርገው በጣሳ ውሃ ላይ የሚደግሞትን ጠሎት በአፍኣ ወይም ድምጣቸውን ከፍ አድርገው የሚደግሞት ውሃውን ጠበል ለማድረግ ብቻ ሳይሆ ጆሯችን ሰምቶ በጆሯችን የገባውም የእግዜር ቃል ሰውነታችንን እንዲቀድሰው ሰምተን እንድንድን ውሃው ወደ ጠበል እንደሚቀየር የኛም ለመንፈሳዊ ሕይወት ውሃ የሆነው ሰውነታችን ተለውጦ እንድነቀደስ ነው፡፡
ስለዚህ ልጆቻችን ቅዳሴ ሲሰሙ፣ እኛ ተሰጥኦ ስንቀበል ቢሰሙ፣ የካህናቱን የሚያብለጨልጭ ልብስ አይተው ቢማረኩና ለምን እንደሆነ ቢጠይቁ፣ በሳምንት አንዴ በየ ቤተክርስቲያኑ እየለመኑ፣ እያቆላመጡ ቃለ እግዜርን በሚስማማቸው መልኩ ለኛም ሆነ ለነሱ የሚያስተምሩ (እንደነ ቀሲስ ሶሎሞን ሙሉጌታ፣ ቦሌ መድኃኔዓለም) መምግራን እግዜር ሳያሳጣን፡ ልጆቻችን እንዲህ ሆኑ ብንል ትርፉ ምንድር ነው….
ሪቶሪካል ኩዌስችን ይሉታል ነጮች፣ መልሱ የሚታወቅ ጥያቄ ከምንጠያየቅና ግራ ከምንጋባ ለኔ እንደሚታየኝ ለዚህ ሁሉ ነገር ማሰርያው መፍትሄ የእኛ ተምሮ፣ መሃይመኖት መመላለስና መኖር ነውና፣ ስለ ሃይማኖታችን ግድ ይስጠን(እንማር)፣ ቦታ ሰጥተን (እናገልግል፣ እንገልገል)፣…
ስንክሳር እየተነበበለትና እያነበበ ላደገ ልጅ፣ ላሳደገም ወላጅ፣ ግብረዶማዊነት ሊደረስበት የማይችል እንኳን የተግባር የሃሳብ መንገድ ነው፡፡
እኛንም ሆነ ልጆቻችንን የትም ቦታ ተከትሎ ልናደርግ ካሰብነው ክፉ ነገር ሊከለክለን የሚችል እግዚአብሔር መንፈስቅዱስ ነውና ለስጋዊ ምግባችን የእነ እገሌን ሱፐር ማርኬት እንደምናጨናንቀው ሁሉ ለመንፈሳዊ ጸጋም ቤተክርስቲያን መሄድ አለብን ባይ ነኝ፡፡
....ግብረስጋ ግንኙነት እኛ ከምናስበው በላይ ከፍተኛ ሃይል አለው! ለዚህም ነው ጠቢቡ እንዲህ ያለን..ምሳሌ5; 20 ልጄ ሆይ፥ ስለ ምን ጋለሞታ ሴት ትወድዳለህ? የሌላይቱንስ ብብት ለምን ታቅፋለህ?.... ኃጥኣንን ኃጢአቱ ታጠምደዋለች፥ በኃጢአቱም ገመድ ይታሰራል !ለምሳሌ እግዚአብሄር ሴትን ሲፈጥር መጀመሪያ እርሷ ጋር ወሲብ የፈጸመው ወንድ ከሌሎች ይልቅ ከርሷ ላይ የበላይነት እንዲኖረው አድርጎ ነው! ለዚህም ነው ጌታ ከጋብቻ በፊት ወሲብን የከለከለው! ብዙ ጊዜ ሴቶች የመጀመሪያ ወዳጅአቼውን እየብደላቸው እንኳን ትተውት ለመሄድ ብርታቱ አይኖራቸውም!ምሳሌ 6;27አመንዝራም ሴት የሰውን ሕይወት ታጠምዳለች።በጉያው እሳትን የሚታቀፍ፥ ልብሶቹስ የማይቃጠሉ ማን ነው?
ReplyDelete28 በፍም ላይ የሚሄድ እግሮቹስ የማይቃጠሉ ማን ነው?
29 ወደ ሰው ሚስት የሚገባም እንዲሁ ነው!32 ከሴት ጋር የሚያመነዝር ግን አእምሮው የጐደለ ነው፤ እንዲሁም የሚያደርግ ነፍሱን ያጠፋል። ዝሙት የሚፈጽሙ ሰዎች ነፍሳቼው ወደ ተለያዩ ሰዎች ስለምትበታተን የወሲብ አለመጣጣም ይከሰትባቼዋል! አሁን የሚፈጽሙትን ወሲብ ከቅድሞው ጋር ማነጻጸራቼው ስለማይቀር ፍቅር መለዋወጥ አቅጦአቼው በወሲብ ለመርካት ይቸገራሉ...
.... ብዙ ሰውች ከጋብቻ በፊት የሚፈጸም ማንኛውም ወሲብ ነፍሳቼውን የሚበታትን እና ከአንድ ሰው ጋር ተወስኖ የመኖር ችሎትአቼውን እንደሚያበላሽ አልገባቼውም! የጋብቻ አንዱ ጥቅም የሰዎችን የወሲብ ስሜት ማርካት ነው!ምሳሌ 5;19 ከጕብዝናህም ሚስት ጋር ደስ ይበልህ። እንደ ተወደደች ዋላ እንደ ተዋበችም ሚዳቋ፥ ጡትዋ ሁልጊዜ ታርካህ፥ በፍቅርዋም ሁልጊዜ ጥገብ! ስለዚህም ነው ሃውርያው ለብዙ ጊዜ ባልና ሚስትን ማለያየትን የከልከለው=1ኛ ወደ ቆሮንቶስ7; 5 ለጸሎት ትተጉ ዘንድ ተስማምታችሁ ለጊዜው ካልሆነ በቀር፥ እርስ በርሳችሁ አትከላከሉ፤ ራሳችሁን ስለ @አለመግዛት ሰይጣን እንዳይፈታተናችሁ ደግሞ አብራችሁ ሁኑ!
ReplyDeleteምክንያቱም ባልም ሆነ ሚስት.. ፍሎጎቷን ሆነ ፍላጎቱን የሚያሟላ ካጡ ወድሌላ ፍለጋ ይሄዳሉና ነው!
.... ግብረ ሰዶማውያን ተመሳሳይ ጾታ ያላቼውን ሰዎች መናፈቅና መመኝት የሚጀምሩት በህጻንነታቼው ወይም በወጣትነታቼው በደረሰባቼው የወሲብ ጥቃት የተነሳ ነው! homosexuality የዚህ ቀጥተኛ ውጤት ነው በጥቃቱ ወቅት መንፈሱ ስለሚተላልፍባቼው NEW! ከዚያም ከላይ እንዳይነው የወሲብ ሃይል ከፍተኛ በመሆኑ በራሳቼው ነጻ መሆን አይችሉም እንዲያውም የወሲብ ጓደኛ ለማግኘት ሲሉ ህጻናት ላይ እንኳ ጉዳት እንዲያደርሱ ይገደዳሉ - እኔ በነሱ አልፈርድም ምክንያቱም መንፈሱ ነፍሳቼውን ስለተዋሃደ ምንም ማድረግ አይችሉም እንግዲህ ይህ መንፈስ ከአንዱ ወደ አንዱ እይተላልፈ ብዙ ግብረ ሰዶማውያንን ያፈራል..
ReplyDelete.... አምላካችን አለማትን የፈጥረው ሲታዘዟቼው ነጻነትን ሲጣሱ ደግሞ እስራትን በሚያመጡ ተፈጥሯዊ እና መንፈሳዊ ህጎች እንዲመሩ አድርጎ ነው!አዎ ግብረ ሰዶማውያንን መፈወስ ካልቻልን በቀር ስለግብረሰዶም በማውራትም ሆነ በማውገዝ ልናቆመው አይቻለንም ባሁኑ ጊዜ ደግሞ በገራችን በሺዎች የሚቆጠሩ ስላሉ ማውገዝ ችግሩን ያባብሰው እንጂ መፍትሄ አያመጣም እንዲያውም እነሱን ለቂም በቀል እና ግብረ ሰዶማውያንን ለማብዛት እና የሂዎት ጉደኛ በበቂ ሁናቴ ለማግኘት ብለው በምስጢር ዘመቻ ህጻነት እንዲደፍሩ ያደርጋቼዋል ... እና መፍትሄው ምንድን ነው?...
ReplyDeleteበጣም ጥሩ ትምህርት ነው
ReplyDelete.... እና መፍትሄው ምንድን ነው?..1. መጀመሪያ ግብረ ሰዶማውያንን አለማግለል ነው!ይህም እነሱ ታሪካቼውን ሳይፈሩን ሳያፈሩ እንዲያወጡ መንፈሳዊና አካላዊ ስነልቦናዊ ፈውስ እንዲገኝላቼው በር ይከፍታል! ምናልባት ይህ ባይሆን እንኳን አንድ ለአንድ እንዲወሰኑ እና ምንም የማያውቁ ጨቅላ ህጻናትን እንዳይደፍሩ ስምምነት መድረስ ይቻላል 2.ቤተክርስቲያን የተሰጣትን ስልጣን ትጠቀም!ቤተክርስቲያን አጋንንትን እንድታወጣ ልጆቿን ከምንኛውም ስነልቦናዊ እና አካላዊ ጉዳት እንድጠብቃቸው አደራ የተሰጣት እንድትገብረው እንጂ እንድታንቀልአፋ አይደለም ቤተክርስቲያን ታዛለች ትዛዝ የሚተገብር እንጂ እንደ አስተያየት = ምክር አይደለም! ስለዚህ ቤትክርስቲያን ከዘመኑ የሚገጥማትን ተግዳሮት የሚያሳልፈውን የእግዚአብሄር ቃል እና መንፈስቅዱስን ልጅቿን ታስታጥቅ..
ReplyDeleteegziyabhar ybarkh diyaqon be ewnet litasebbet yemigeba guday new ethiopia ejochuwan wede egziyabhar tzeregalech !!!
ReplyDelete...መጽሐፍ ቅዱስ፣ ሰዎች ተገቢ ላልሆኑ የፆታ ፍላጎቶች ላለመሸነፍ ከልባቸው እስከፈለጉ ድረስ ከእነዚህ ነገሮች መራቅ እንደሚችሉ ማረጋገጫ በመስጠት አምላክ የሰው ልጆችን እንዳከበራቸው ይገልጻል።—ቆላስይስ 3:5የግብረ ሰዶማዊነት መከሰቻ ምክንያቶች
ReplyDelete- በAባትና በልጅ መካከል የሚኖር ጤናማ ያልሆነ ግኑኝነት
- ይልቁኑ በወንዶች የሚፈጸሙ ግብረ ሥጋዊ ነውጦች ወይም
ሙከራዎች
- ልቅ ለሆኑ የግብረ ሥጋ ግኑኝነት ፊልሞች መጋለጥ...ኑ ዋናው ምክንያት ግን ለግብርእሰዶማዊ ጥቃት መጋለጥ ነው ችግሩን አስፈሪ የሚያረገው ግን
- ተቃራኒ የሆኑ መንፈሳዊ ተጽEኖዎች (ግብረ ሰዶማዊ
“ጳጳሳትንና ቀሳውስትን” መሾም)
- የመገናኛ ብዙኀን ተጽEኖ (ሁሉን የማቻቻል ሲባል የሚመጣ)
- የራስ ግላዊ ጠባይ፤ ጎጂ የሆነ Aካላዊ ገጽታ
- ወደ ተቃራኒ ጾታ ለመቅረብ መፍራት ወይም Aለመቻል...ሲሆኑ ዋናው ምክንያት ግን ለግብርእሰዶማዊ ጥቃት መጋለጥ ነው ችግሩን አስፈሪ የሚያረገው ግን ሙሉ በሙሉ ሊባል በሚቻል ሁኔታ የተደፈሩ ሁሉ ግብረ ሰዶማዊ ይሆናሉ - ስለዚህ በዚህ ጉዳይ ላይ ገብረስእዶማውያን ራሳቼው የሚሳተፉበት አውደ ጥናት ማዘጋጄት ያስፈልጋል-..
.. አምላካችን አለማትን የፈጥረው ሲታዘዟቼው ነጻነትን ሲጣሱ ደግሞ እስራትን በሚያመጡ ተፈጥሯዊ እና መንፈሳዊ ህጎች እንዲመሩ አድርጎ ነው!SEX or ‘Making Love,’
ReplyDeleteis the complete intimate connection
between man and woman, where they
both feel an inseparable ability to stay
together because of the ‘soul ties’ that
they have formed through their sexual
union.ኦሪት ዘፍጥረት2;24 ስለዚህ ሰው አባቱንና እናቱን ይተዋል፥ በሚስቱም ይጣበቃል፤ ሁለቱም አንድ ሥጋ ይሆናሉ።
ፈጣሪሽ ባልሽ ነው፥ ስሙም የሠራዊት ጌታ እግዚአብሔር ነው፤ የእስራኤልም ቅዱስ ታዲጊሽ ነው፥ እርሱም የምድር ሁሉ አምላክ ይባላል።.. ከዚህ ጥቅስ የምንረዳው ትዳር ከትስስሮች ሁሉ ከፍተኛው ጥምረት መሆኑን ነው ስለዚህም ከጌታችን ጋር ያለን ግንኙነት በባልና መልክ የተገለጠው!ሁለት ሰዎች በጋብቻ ሲጣመሩ ሁለት አንድ ይሆናሉ!sex ሁለት ሰዎችን እርስ በርስ የሚያስተሳስር ከሆነ ተፈጥሩዊ ያልሆነው ግብረ ሰዶምም ሆነ ዝሙት እንዲሁ የዚያች ሰው ነፍስ አብሯት ግንኙነት ከፈጸመው ሰው ጋር ሁሉ ትተሳሰራለች ዘፍጥረት 34 : 1
ለያዕቆብ የወለደችለት የልያ ልጅ ዲናም የዚያን አገር ሴቶች ልጆችን ለማየት ወጣች። 2.፤ የአገሩ አለቃ የኤዊያዊ ሰው የኤሞር ልጅ ሴኬም አያት፤ ወሰዳትም ከእርስዋም ጋር ተኛ አስነወራትም።
3፤ ልቡናውም በያዕቆብ ልጅ በዲና ፍቅር ተነደፈ፥ ከዚህ ታሪክ ምን እንረዳለን? አዎ ሴኪም ልጅቱን መጀመሪያ አልወደዳትም ከደፈራት በኋላ ግን ልቡ እርሷን መናፈቅ ጀመረ ምክናያቱም አስገድዶ በምድፈርም በኩል ቢሆን ነፍሶቻቼው ተሳስረዋል ሰው ከመጀመሪያው ወዳጁ ጋር ግንኙነት ካረገ በሁዋላ ግማሽ አካሉ ከወዳጁ ጋር አንድ ስለሆነ ከዚያ በሁዋላ በሚደረግ ግንኙነት እንደመጀመሪያው እርካታን አያገኝም ምክንያቱም SPRITUALBOND ስለተፈጠረ ነው Every evil spirit that Party One possesses will travel through to the other Party as the two become one flesh in a manner that the Creator only intended to occur in marriage! - ስለዚህም አንድ ህጻን ሲደፈር በዳፋሪው ውስጥ ያሉት መናፍስት ሁሉ ወደ ልጁ ይተላለፋሉ ማለት ነው ከዚያ በሁዋላ ምንም ያህል ጥረት ቢያደርግ ከመንፈሱ እስኪላቀቅ ድረስ ከHOMOSEXUALITY ነጻ መሆን አይችልምግብረ ሰዶማውያን ተመሳሳይ ጾታ ያላቼውን ሰዎች መናፈቅና መመኝት የሚጀምሩት በህጻንነታቼው ወይም በወጣትነታቼው በደረሰባቼው የወሲብ ጥቃት የተነሳ ነው! homosexuality የዚህ ቀጥተኛ ውጤት ነው በጥቃቱ ወቅት መንፈሱ ስለሚተላልፍባቼው NEW! ከዚያም ከላይ እንዳይነው የወሲብ ሃይል ከፍተኛ በመሆኑ በራሳቼው ነጻ መሆን አይችሉም እንዲያውም የወሲብ ጓደኛ ለማግኘት ሲሉ ህጻናት ላይ እንኳ ጉዳት እንዲያደርሱ ይገደዳሉ - እኔ በነሱ አልፈርድም ምክንያቱም መንፈሱ ነፍሳቼውን ስለተዋሃደ ምንም ማድረግ አይችሉም እንግዲህ ይህ መንፈስ ከአንዱ ወደ አንዱ እይተላልፈ ብዙ ግብረ ሰዶማውያንን ያፈራል.
አካላዊ(Physical) መደፈራችንና ስብራታችን ከዚህ የከፋው አስቀድሞ ያለው የመንፈሳዊ (Spritual) መደፈራችንና ስብራታችን መገለጫ ነው፡፡ሰው አለሙን ሁሉ ቢያተርፍ ነገር ግን አንድያ ነፍሱን ቢያጣ ምን ይጠቅመዋል እንደተባለው ላለፉት 22 ዓመታት ይህች ድሃ ነገር ግን የተቀደሰች ሀገር ለዘለቄታው ብዙ የማይተቅማትን ብዙ አማላይ የሆኑ ብልጭልጭና አርተፊሻል ነገሮችን አግበሰበሰች ነገር ግን በሬ ሆይ በሬ ሆይ ሳሩን አየህና ገደሉን ሳታይ አይነት ሆነና ይህች ሀገር በአስገድዶ ደፋሪዎች በረቀቀና በተቀነባበረ መንገድ እየተደፈረች (ህፃናትን በከረሜላ እያታለሉ አስገድዶ የመድፈር ያህል ማት ነው) ቀስ በቀስ ወደ ጥፋት እያመራች እንደሆነ ብዙዎቻችን በቅጡ አልገባንም፡፡ ክብራቸው በነውራቸው ነው የተባለው ትንቢት መፈፀሚያ ሆነን እንደተባለው እውነት ከሆነ በBig Brother Africa ቆነጃጅት ሴቶቻችን ለተራ ዝናና ገንዘብ ብለው በአደባባይ ከውጪ ሰዎች ጋር ወሲብ ሲፈፅሙ የመታየታቸው ቅኔ ምንድን ነው?ቅኔው ደግሞ ይህች ታሪካዊትና ቅድስት ሀገረ ኢትዮጵያ የባእዳን ሰይጣናዊ ስራ መፈንጫ ሆና አንገቷ ታንቆ አካላዊና መንፈሳዊ አስግድዶ መድፈር(ህፃናትን በከረሜላ እያታለሉ አስገድዶ የመድፈር ያህል ማለት ነው) እየተፈፀመባት መሆኑን ነው፡፡ይህ አይነት አሳፋሪና አሳዛኝ ታሪካዊ አጠቃላይ የትውልድ ዝቅጠት እየተከናወነ ባለበት ሁኔታ ውስጥ ወያኔ በባእዳን እርዳታና ብድር ገንዘብ ኢትዮጵያን አለማሁኝ የሚለው ነጠላ ዜማ እናትና አባት ጨቅላ ልጃቸውን ለዝሙትና አስገድዶ ደፋሪዎች እየሸጡ ገንዘብ እንደሚቀበሉት አይነት ነውና ወያኔ እንደ አገዛዝ በታሪክም በፈጣሪም ዘንድ ለዘላለም ተጠያቂ ነው፡፡ይህ አሳፋሪና አሳዛኝ ሰይጣናዊ ክስተት ደግሞ ዝም ብሎ በዘፈቀደ በአጋጣሚ የተፈጠረ ነገር ሳይሆን በረቀቀና በተቀነባበረ መንገድ ይህንን አስነዋሪ ስራ የሚሰራ በህቡእ በደንብ የተደራጀ አካል አለ፡፡
ReplyDeleteገንዘብ የሃጢያት ሁሉ ምንጭ ነውና ይህ ሁሉ አሳፋሪና አሳዛኝ ሰይጣናዊ ነገር እየተደረገ ያለው ደግሞ በሌሎች ብዙሃኖች ጥፋትና ኪሳራ ጥቂቶች ተደላድሎ ለመኖር ከማሰባቸው ልቅ የሆነ ስግብግብነት የመነጨ ነው፡፡ነገር ግን ጥፈቱ ስልጣን ገንዘብ ዘር ሃይማኖት እውቀት ወዘተ ሳይለይ የእያንዳንዱን ቤት በየተራ ያንኳኳል፡፡መፍትሄው ደግሞ ወደ ፈጣሪ መፆም መፀለይና ህዝቡን ማስተማር ማንቃት መታገል ብቻ ነው፡፡
እግዚአብሄር ኢትዮጵያን ይባርክ!!!
እኔን በጣም የሚገርመኝ የኢትዮጵያ መንግስት የሀገርን ታሪካዊ ገፅታ በመጠበቅ ረገድ ለጥ ብሎ መተኛቱ ነው፡፡ባህላዊ እሴቶቻችን ኢትዮጵያዊ ማንነታችን እነደመሆናቸው መጠን ህገ መንግስታዊ ድንጋጌ ያላቸውና በዚሁ መሰረት የሚጠበቁ መሆን አለባቸው፡፡አሁን እየሆነ ካለው ነገር የሚንረዳው ግን ባለቤት እንዳጡ ነው፡፡ ለምሳሌ ባለፉት ሳምንታት የመነጋገርያ አጀንዳ ሆኖ የነበረውና በማወቅም ይሁን ባለማወቅ በአለም የቅሌት ቅርጫት ውስጥ እንድንሰነብት ያደረገችንን ግለሰብ ጉዳይ መንግስት ቢንስ ሀገራችንን እንደማትወክል መግለጫ ያወጣል ከቻለም በህግ ይጠይቃታል ብዬ ስጠብቅ በዝመታ መታለፉ ብዙ ተከታዮችን አፍሪ፤ እደጊ ተመንደጊ እንደማለት ይኮጠራል፡፡ስለዚህ ዳኒ በአጭሩ ማለት የምፈልገው የንጉስን ጆሮ ማግኘት ከባድ ቢሆም መንግስት ለባህላችንና ለማንነታችን ትኩረት እንዲሰጥ፤ ህገ መንግስታዊ ከለላና ተቋማዊ አደረጃጀት ኖሮት ጥበቃ እንዲደረግልት አቤት ማለት ያስፈልጋል፡፡
ReplyDeleteDiakon Danieal huligize astemarina wikitawi tsihufochin iyetsafk silemitasnebiben Egzeabher Amilak yibarkih
ReplyDeleteዳኔ ትልቅ የክረምት የቤት ሥራ ሰጠኸን ፤ ለዚያውስ ፈጣሪይ በዜያ በተለመደው ጥበቡ ካልረዳን ምን ማድረግ ይቻላል። ችግሩ የከፋ ዓለም ገንዘብ ሴገዛት ነው።
ReplyDeleteጌታ ሆይ እባክህ ቁጣህን በምህረት ቀይረው።
It is a gay movement! Someone is always behind it. They are funding it...supporting it...they want to be celebrated. I am not that worried. They cannot do that in Ethiopia, unless they want the gay holocaust to be repeated once again in history. We just have to protect from liberals taking power in the country. Lets give vote for conservatives...whether be it a Muslim or Christian.
ReplyDeletehttp://www.youtube.com/watch?v=tBG7bUBqbj8
Dear Maranata,
ReplyDeleteDo not be ridiculous. You are going to vote for conservatives, who do not care about the education of your children, the state of affairs of your poor neighbors, the state of affairs of immigrants and their families to get your vote over something you totally misunderstand?
Embarrassed,
I dont care to all the concerns (affairs) you mentioned. More than anything, I am concerned to social matters. It is rather embarrassing to vote leaders who are impenitent and morally deprived....those who do not know (do not care to) what is "right" and what is "wrong". We need good social engineers!
DeleteThanks for the comment but the "Dear" wasn't really important. I am not your dear.
Dn Daniel,
ReplyDeleteGuys like you disgust me. You are one delusional individual who considers himself as I know everything genius. First your story is completely fiction that can convince only ignorant and imbecile individuals. Second the solutions that you put in your fictional story doesn't work for Ethiopia. Do you know the penetration rate of Facebook in Ethiopia? it is 1.0% and how much proportion is for kids less than 18 yrs old? And to all the individuals concerned with homosexuality in Ethiopia please try to understand the difference between homosexuality and pedophilia.
I don't understand. Are you simply to negate Dn Daniel or is there any thing that you want to share with us. Ofcourse you can confront Dn Daniel based on your evidences but i don't think that you can stay in discussion with a complete anti verbs. What is facebook here alone here. 1%? It can be! I don't have clue. In fact 85% of our society is already in rural which has little access to facebook or other e-media. Of the urban inhabitant 1% Ethiopian population still is too big. That over 5% of the urban. As a contaminant 1% is already too much. What do you want to tell us in your last statement. What is pedophilia? The issue that Dn. Daniel raise here is completely homosexuality not pedophilia. Why you wan to confuse things. Yet, pedophilia is an other mental disorder.
Deleteyou are talking nonsense. read it again and try to understand it. this is burning issue which everyone of us should be concerned. don't deny the reality Daniel trying to uncover about. if you don't like the author stay away from his website!
DeleteDon't take me wrong wedajochie. Daniel is becoming an important voice in our society. He should have been more careful about his posts. The story he wrote is simply his imagination. He tried to write a film script not the reality. That is what I am opposing. Homosexuality is not a sickness that you diagnose or abnormality. It is just a different behavior of individuals. Don't try to judge these individuals with your shoe. Your moral judgment (which obviously originates from your religion) might not apply to them. Just accept differences. His And I mention pedophilia after reading some of the comments plus “ …….. ሌሎች ግብረ ሰዶማውያን በልጆቹ ላይ ይህንን መሰል ተግባር ሲፈጽሙባቸው ……” This is pedophilia not homosexuality. The majority of such act is performed by the heterosexuals, he could have googled it. If you want to aware the public that is good, but you have to base that on facts and contexts. Otherwise, it is simply a hate fictional message that what the post is. Homosexuality is been in the picture since antiquity(we can mention many examples). Can Daniel give us any evidence that the Internet and the Facebook did aggravate the homosexuality in Ethiopia? Can anybody give us that evidence for that matter?
Deleteወንድ የእውነት ሰው የምልህ ይህን ለመፈታት ጥረት ካደረክ ነው እስከመጨረሻው የሚደርስ፡ ጥረት። አንድ ችግር ስበህ መፍታት ስትችል። እስኪ ይህቺን ወስደህ especialized አድርግባት። ወላጆችን አስተምር። ትምህርት ቤቶችን ተከታተል። ገና ሳይጠና በእንጭጩ እያለ ስራበት። እግዚአብሔር ይርዳህ። I ll do my share. i said so bse i thought u can use all ur circle of influence.
ReplyDeleteIn 1960, every American state had anti-sodomy laws, many of which prohibited intimateacts between persons of the same sex. Homosexuals hid their actions to avoid prosecution. However, in 1969 homosexuals in New York rioted after police raided the Stonewall Inn, a “gay bar.” This led to the formation of the “gay liberation” movement, which has worked for decades to pass anti-homosexual-discrimination laws.
ReplyDeletePro-”gay marriage” lawsuits began to be filed over four decades ago. Although not nationally publicized, between 1970 and 1973, courts in Kentucky, Minnesota and Washington denied marriage licenses to same-sex couples that filed lawsuits to obtain them. Yet the intellectual stance on homosexuality began to change. It was in 1973 that the American Psychiatric Association stopped listing homosexuality as a mental disorder.
Americans have come to tolerate, embrace and even champion many things that would have horrified their parents’ generation-from easy divorce and unrestricted abortion-on-demand to extreme body piercing and teaching homosexuality to grade-schoolers. Does that mean today’s Americans are inherently more morally confused and depraved than previous generations? Of course not, says veteran journalist David Kupelian. But they have fallen victim to some of the most stunningly brilliant and compelling marketing campaigns in modern history.The Marketing of Evil reveals how much of what Americans once almost universally abhorred has been packaged, perfumed, gift-wrapped and sold to them as though it had great value. Highly skilled marketers, playing on our deeply felt national values of fairness, generosity and tolerance, have persuaded us to embrace as enlightened and noble that which all previous generations since America’s founding regarded as grossly self-destructive-in a word, evil.
The battle of world views and many of today’s most contentious issues receive appropriate attention. Same sex marriages, pedophilia and the legalization of homosexuality are among the many issues discussed. Promiscuity is itself cited as being portrayed as just another element of “freedom”.
Read how the Homosexual Agenda has managed to control America’s media to turn our thinking of homosexuals as sinners and deviants to poor, poor gays that have been so misunderstood for so long.
There was a time when Americans knew that homosexuals were not born that way, but rather had their normal identity-gender redirected and disturbed via early childhood experiences; typically, an “attack” by a homosexual or other deviant, possibly a family member.
But homosexuals have managed to hoodwink the US media (and ex-Presidential candidates like Kerry) to buy into the lie that they are born that way. Concomitantly, homosexual deviant behavior is protected –so that they can now freely multiply. But God is not amused.
Another example, few of us realize that the widely revered father of the “sexual revolution” (Kinsey) has been irrefutably exposed as a full-fledged sexual psychopath who encouraged pedophilia. Also, did you know that giant corporations voraciously competing for America’s $150 billion teen market routinely infiltrate young people’s social groups to find out how better to lead children into ever more debauched forms of “authentic self-expression.”
God Told us These Times Would Come!
በስመ አብ
ReplyDeleteምንድንው ጉዱ
ይህ የምሰማውን ነገር በልጆቼ ላይ እንዳላይ በእውነት ጠዋትና ማት ነው የምጸልየው
...የግብረ ሰዶማውያኑ ኑዛዜ
ReplyDeleteመሰንበቻውን መቐለ ከተማ ለንባብ የበቃው የገጣሚ ግርማይ ገብሩ ‹‹እሞኸ›› የትግርኛ የግጥም መድበል በጭብጥነት ካነሳቸው ማኅበራዊ ቀውሶች አንዱ ግብረ ሰዶማዊነት ነው፡፡
ሦስት ጉልቻ ሲመሠረት ‹‹የአብርሃምና ሳራ ጋብቻ ይሁንላችሁ›› የሚለው ትውፊታዊው ዜማ በሁለት ተቃራኒ ጾታዎች መካከል ስለሚደረገውና ስለሚፈጸመው ቅዱስ ጋብቻ ነው፡፡
ማጠናከርያ ነው፡፡ አሁን አሁን በዓለም የሚታየው በአገሪቱም እየተከሰተ ያለው አዳምና ሔዋንነትን ሽሮ፣ አብርሃምና ሳራነትንም ትቶ ወደ አብርሃምና አብርሃምነት እየተሄደ ያለው የጥፋት መንገድ ግብረ ሰዶማዊነት እየታየ መሆኑን ለማሳየት ገጣሚው ‹‹ሕንከተ ኣልቦ›› የሚል ርእስ ያለውን ግጥሙን ከትቦታል፡፡
‹‹ብኣብርሃምን ሳራን
ቃና ዘገሊላ
ዝጀመረ ማሕላ
ዝደመቐ መርዓ
አብ ጽላል ዋሪዓ
ኮይኑ ግን …
ንቡር ኣዳም ሄዋን
ንሳራ ሓዲጉ ሞት ዝፀወዖ
ኣብርሃም ንኣብርሃም
ከመይ ኢሉ ይመርዖ፡፡›› በግርድፉ ሲተረጐም በአብርሃምና ሳራ በቃና ዘገሊላ የተጀመረ በመሐላ የፀና ጎጆ በዋርካ ጥላ ስር የደመቀ ሠርግ፤ በአዳምና ሔዋን የተጀመረውና የተመሠረተው ሳራን ትቶ ሞትን ጠርቶ አብርሃም ለአብርሃም እንዴት ብሎ ይጋባል? ብሎ የሚጠይቅ ነው፡፡ ይኸው እኩይ ድርጊት ግን፣ ፀረ ተፈጥሮ ተግባር ግን መፈጸሙን፣ እየተፈጸመ መሆኑን የሚያሳይ ሁነት ሰሞኑን አዲስ አበባ ላይ ለዕይታ በቅቷል፡፡
‹‹አዲስ አበባ ውስጥ ግብረ ሰዶማዊነት ተስፋፍቷል፡፡ በአንዳንድ ዩኒቨርሲቲዎችና የከፍተኛ ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤቶች፣ በየመንደሩ፣ በየሥርቻው፣ በየጓዳውና ጉድጓዳው ራሳቸውን ደብቀው ያደፈጡ ሁሉ ቢቆጠሩ ብዛታችን ያደላል፡፡ መጠሪያ ስማችን ጌይ ወይም ግብረ ሰዶማዊ የሚል ሳይሆን ‘ዜጋ’ የሚለው ነው፡፡ በዚህ ሕይወት ውስጥ ያልገቡ ሌሎች ወገኖችን ደግሞ ‹‹ቀጥ›› በሚል እንጠራቸዋለን፡፡››
ይህንን የተናገሩት ከሰባት እስከ 32 ዓመት ድረስ ሕይወታቸውን በግብረ ሰዶማዊነት ያሳለፉት ግብረ ሰዶማውያንና ግብረ ሰዶማውያት (ወንዶችና ሴቶች)፣ ‹‹ዝምታው ይሰበር ትውልድ ይዳን በእኛ ይብቃ›› በሚል ርዕስ በተዘጋጀ ዶክሜንተሪ ፊልም (ቪሲዲ) ውስጥ ባካሄዱት ቃለ መጠይቅ ላይ ነው፡፡
በቸርችል ሆቴል የስብሰባ አዳራሽ ውስጥ በተከናወነው ሥነ ሥርዓት ላይ ‹‹ስለኢትዮጵያ ዝም አንልም ግብረ ሰዶማዊነት በኢትዮጵያ የ666 አሠራር›› የሚል ታካይ ርእስ ባለውና ለምረቃ በበቃው በዚሁ ፊልም ውስጥ ይህንኑ ቃለ መጠይቅ ካካሄዱት ከእነዚህ ግብረ ሰዶማውያን ማብራሪያ ለመረዳት እንደተቻለው ሕጋዊና መደበኛ ሚስት አግብተው፣ ትዳር መስርተውና ልጆች ወልደው በሽምግልና ዕድሜያቸው ግብረ ሰዶም የሚፈጽሙ አዛውንቶች አሉ፡፡ አንዳንድ ጊዜ ‹‹አባባ መሽቷል እባክዎን ወደ ቤትዎ ሂዱ›› እያሉ ወጣት ግብረ ሰዶማውያን ይቀልዱባቸዋል፡፡ ይሳለቁባቸዋል፡፡ እነዚህም አዛውንቶች ታዋቂነታቸው በ‹‹ዜጎች›› ዘንድ ብቻ ስለሆነና በአካባቢያቸው ማኅበረሰብ ዘንድ የሚታወቁት ባለትዳርና የልጆች አባት ስለሆኑ ከማኅበረሰቡ ዘንድ እንዳይገለሉና ተከብረው እንዲኖሩ አድርጓቸዋል፡፡
የእምነት ቃላቸውን ከሰጡት ግብረ ሰዶማውያን መካከል በቅጽል ስሙ ‹‹ኤሊያና›› በሚል መጠሪያ የሚታወቀው ወጣት፣ ግብረ ሰዶም መጀመርያ የተፈፀመበት በሐዋሳ ከተማ የሰባት ዓመት ሕፃን ሳለ ነበር፡፡ በዚህ ሕይወት ውስጥ መኖር ከጀመረ 32 ዓመታትን አስቆጥሯል፡፡ እስካሁን ባሳለፈው ሕይወት ውስጥ ለወሬም የማይመች፣ ከባህል ውጭ የሆነ፣ ሕይወትን እስከመጥላት የሚያደርስና አሰቃቂ የሆነ ወሲብ ከተመሳሳይ ጾታ ጋር ሲፈጸም እንደኖረ ነው የተናገረው፡፡
ግብረ ሰዶማውያን የሚፈልጉትን ቆንጆ ወንድ አንዲት ሴት ይዛባቸው ከሄደች ወይም ካወጣችው ‹‹ዓይነጥላ›› ወሰደችብን እያሉ እንደሚያማርሩ ያወሳው ኤሊያና፣ በድሬዳዋ፣ በጅቡቲ፣ በየመንና በሳዑዲ በሚገኙ የተለያዩ ከተሞች ይህንኑ የግብረሰዶም ሥራ ያከናውን እንደነበርም አልሸሸገም፡፡ ጅቡቲ የገባው ከድሬዳዋ እስከ ደዋሌ ድረስ በባቡር ከዚያም እስከ ጅቡቲ ደረስ በእግሩ ለአምስት ቀን ያህል ከተጓዘ በኋላ ነው፡፡ ከጅቡቲም በአንድ የሞተር ጀልባ ተደብቆ ወደ የመን እንደተሻገረና በመቀጠልም ሳዑዲ እንደገባ አመልክቷል፡፡
‹‹በአገር ውስጥ በተለያዩ ቦታዎች የአምስት ተመሳሳይ ጾታ ያላቸው የግብረ ሰዶማውያን ሠርጎችን አይቻለሁ፡፡ ይህን ዓይነቱንም ሠርግ መንግሥት ወይም ማዘጋጃ ቤትና ባህል አያውቀውም፡፡ እኛው ራሳችን ነን የምንፈጽመው፡፡ ይህም ሆኖ ፍቅርን ስለማናውቅ በጋብቻ ፀንተን አንቆይም፡፡ ጋብቻው ግፋ ቢል የሚቆየው ለሦስት ወራት ያህል ብቻ ነው፤›› ብሏል፡፡
ሚስት የሚሆን ወንድ በሠርግ ሥነ ሥርዓቱ ቀን ቅንድቡን ተቀንድቦ፣ ቻፕስቲክ ተቀብቶ፣ ፊቱ ላይ ማድረግ የሚገባውን ሜክአፕ ሁሉ አድርጎ፣ ፀጉሩን ተሠርቶና ቬሎ ለብሶ ይቀርባል፡፡ በሥነ ሥርዓቱም ላይ ኬክ እንደሚዘጋጅ ነው የተናገረው፡፡
ሠላሳ ሁለት ዓመታት ያህል በግብረ ሰዶም ሕይወት የቆየ፣ ስምንት ጊዜ ድል ባለ ሠርግ አግብቶ የወንድ ሚስት የነበረና በቅጽል ስሙ ‹‹አጠለል›› እየተባለ የሚጠራው ሌላው አስተያየት ሰጪ ደግሞ ግብረ ሰዶማዊነትን መተዳደሪያው አድርጎ የያዘው ሲሆን፣ ይህንንም የጀመረው የስምንት ዓመት ሕፃን ሳለ ነው፡፡ የሴት ሚስት ላለውና በዚህ ላይ ደግሞ 17 የወንድ ሚስቶች ካሉት ግብረ ሰዶማዊም ጋር ትዳር ለመጀመርያ ጊዜ ‹‹17ኛ የወንድ ሚስት ሆኜ ነው ያገባሁት›› ሲል አጠለል ይናገራል፡፡.....http://www.ethiopianreporter.com/index.php/other-sections/social-affairs/social/item/2426-%E1%8B%A8%E1%8C%8D%E1%89%A5%E1%88%A8-%E1%88%B0%E1%8B%B6%E1%88%9B%E1%8B%8D%E1%8B%AB%E1%8A%91-%E1%8A%91%E1%8B%9B%E1%8B%9C
...የግብረ ሰዶማውያን መለያቸው ከአለባበሳቸው እንደሚጀምር ይናገራል፡፡ ሁልጊዜ ቁምጣ ሱሪ እንደሚያደርጉ፣ ጠባብ ስኪኒ እንደሚያዘውትሩ፣ ጠልጠል ያለ ቦዲ ቲ ሸርት በመልበስ እምብርት እያሳዩና ያለ ካልሲ ጫማ እያደረጉ እንደሚሄዱ፣ ፀጉራቸውን ሊሞዚ መቆረጥ፣ ጆሯቸውን በተለየ ቦታ ላይ በመበሳት ጌጣ ጌጥ ማስገባትና ሎቲ ማንጠልጠል ናቸው፡፡ ከውጭ አገር የሚረዷቸውም ሰዎች አሉ፡፡ በተለይ ዳያስፖራዎች የጠለልን አድራሻ ይዘው ነው የሚመጡት፡፡ ሲጠሩት ይቀበላቸዋል፡፡ በኢንተርኔትም የሚገናኙበት መንገድ አለ፡፡ በዚህም የተነሳ ደንበኞቻቸው ሲመጡ አይቸገሩም፡፡ በሚፈልጉበት ቦታ አገልግሎት ያገኛሉ፡፡
ReplyDelete‹‹ሪች›› በመባል የምትጠራዋ ሌላው ግብረ ሰዶማዊት (ሌዝቢያን) ወደዚህ ሕይወት ውስጥ የገባችው በጓደኛዋ ግፊት እንደሆነ፣ በዚህም ሕይወት ከገባች ስምንት ዓመት እንደሆናትና መተዳደሪያዋም ይኸው እንደሆነ ገልጻለች፡፡ ሁለት ቋሚ የሴት ደንበኞችም እንዳሏት ተናግራለች፡፡ አንደኛዋ ደንበኛዋ አዲስ አበባ ውስጥ ኦሎምፒያ አካባቢ፣ ሁለተኛዋ ደንበኛዋ ደግሞ በሐዋሳ ከተማ ይኖራሉ፡፡ በጠሩዋት ቁጥር ትሄድላቸዋለች፡፡፡ ጠሪዎቿም በጣም ሀብታሞች እንደሆኑ ነው የተናገረችው፡፡ በዚህም እርካታ እንደምታገኝ፡፡ ከተመሳሳይ ጾታዋ ጋር ካልሆነ በስተቀር ለወንድ ወይም ለተቃራኒ ጾታ ፍላጎት እንደሌላት አስረድታለች፡፡
ብሩክቱ ሌላዋ ግብረ ሰዶማዊት ናት፡፡ ሪታ የምትባል ክልስ የልጅነትና አብሮ አደግ የሆነች ጓደኛ ነበረቻት፡፡ በልጅነታቸው ትምህርት ቤት ሲገናኙና ከትምህርት መልስ ወደየቤታቸው ለመሄድ ሲለያዩ ይሳሳማሉ፡፡ ይህን ዓይነት ሁኔታ ቢያዘወትሩም የልጅነት ነገር እንጂ ወደ ሌላ ስሜት አይመራቸውም ነበር፡፡ ከዓመት ዓመት እያደጉና ነፍስ እያወቁ ሲመጡ በመካከሉ ሪታ ወደ ኢጣሊያ አቀናች፡፡
ሪታ ከሄደችበት ወደ ኢትዮጵያ ስትመለስ ግን ተለውጣ መጣች፡፡ የመሳሳማቸው ሁኔታ ወደ ልጅነት መንፈስ መሄዱ ቀርቶ ወደ ወሲብ ቀስቃሽነት ተሻገረ፡፡ በዚህም የተነሳ ውለው ሲያድሩ ፍቅር መሠረቱ፤ ‹‹እወዳታለሁ ትወደኛለች፣ ከእሷ ጋር ግንኙነት ሳደርግ ታስደስተኛለች፡፡ በዚህ ሕይወት ውስጥ ከገባሁ ሰባት ዓመት ሆኖኛል፤›› ብላለች ብሩክቱ፡፡
ሁሉም ወንዶችና ሴቶች ግብረ ሰዶማውያን ኤችአይቪ ፖዘቲቭ እንደሆኑ፣ በዚህ ላይ ደግሞ የሥነልቡና ችግርና የአአዕምሮ ጭንቀት እንዳጋጠማቸው፣ በተለይም ኤሊያና የኪንታሮት በሽታ እንዳደረበት፣ ሁሉም ከዚህ አስከፊና አስነዋሪ ሕይወት ለመውጣት እንደሚፈልጉ በየተራ በሰጡት አስተያየት አረጋግጠዋል፡፡
ሰኔ 23 ቀን 2005 ዓ.ም. በተከናወነው የዶክመንተሪ ፊልሙ የምረቃ ሥነ ሥርዓት ላይ የሁሉም እምነቶች ተከታዮች፣ አባት አርበኞች፣ ታዋቂ ግለሰቦች፣ የኪነ ጥበብ ባለሙያዎች፣ አትሌቶችና ጥሪ የተደረገላቸው እንግዶች ተገኝተዋል፡፡ በዚህም ጊዜ መምህር ደረጀ ነጋሽ (ዘወይንዬ) የማኅበረ ወይንዬ አቡነ ተክለሃይማኖት ሊቀመንበርና የፊልሙ ዋና አዘጋጅ ዓላማውን ሲገልጹ በአገሪቱ እየተከሰተ ያለው ግብረ ሰዶማዊነት በምን ደረጃ ላይ እንደሚገኝና ትውልድንም ምን ያህል እየጎዳ እንዳለ ለማስገንዘብ ነው ብለዋል፡፡
ሦስት ዓመት በፈጀው ጥናታቸው የተገነዘቡት ነገር ቢኖር ከግብረ ሰዶማውያን መካከል አንዳንዶቹ ይህን ድርጊት ሕጋዊ እናደርገዋለን ብለው የሚዝቱና፤ ከፊሎቹ ደግሞ በተቃራኒ ድርጊቱ ለሕይወት ጎጂ በመሆኑ መውጣት አለብን ብለው የወሰኑ መኖራቸውን ነው፡፡
የኢትዮጵያ የወንጀል ሕግ አንቀጽ 6/29 ግብረ ሰዶም ወንጀል መሆኑን ይደነግጋል፡፡ አንቀጽ 6/32 ደግሞ በዚህ ተግባር የተገኘ ከቀላል እስከ እስከ ዕድሜ ልክ በሚደርስ ያስቀጣል ይላል፡፡ መምህር ደረጀ እንደሚሉት፣ የወንጀል ሕጉ ግብረ ሰዶምን ቢከለክልም ግብረ ሰዶማዊነት በአገሪቷ በድብቅ እየተስፋፋ ነው፡፡ ራሳቸውን አጋልጠው የሚወጡ ሰዎች ቢኖሩም ራሳቸውን ባላጋለጡት ተፅዕኖ ያደርስባቸዋል፡፡
ዶክመንተሪ ፊልሙ በኢትዮጵያ ግብረ ሰዶማዊነት መኖሩን በግልጽ በሚመሰክሩ ሰዎች አማካይነት ለመንግሥትና ለኅብረተሰቡ ማሳወቅና ከድርጊታቸው ይወጡና ይታቀቡ ዘንድ ሁሉም እንዲረባረብ ጥሪ ለማቅረብ ነው፡፡
በፊልሙ ወቅታዊ ሞቅታን ፈጥሮ መለያየት እንደማያስፈልግ የሚናገሩት መምህር ደረጀ፣ በሕፃናት ላይ ግብረ ሰዶማዊ ጥቃት የመፈፀም አካሄድ የሚከተሉትን ግብረ ሰዶማውያን ከወዲሁ ለማቆም በግለሰብ ደረጃ ሳይሆን በሥነ ምግባር ማኅበር ተደራጅቶ በቀጣይነት መሥራት ያስፈልገዋል ብለዋል፡፡
በግብረ ሰዶም ሕይወት ለብዙ ዓመታት ማሳለፋቸውን በመጥቀስ የሕይወታቸውን እውነታ ለገለጹት የቀድሞ ግብረ ሰዶማውያን ከችግር የተነሳ መልሰው እንዳይገቡበት ኅብረተሰቡና መንግሥት ሊረዷቸው እንደሚገባም ተናግረዋል፡፡
በኢትዮጵያ ግብረ ሰዶማዊነት እየተስፋፋና ግብረ ሰዶማዊ ጥቃትም እየተፈጸመ ስለሆነ ድርጊቱ ከመስፋፋቱና ‹‹ለኛም መብት ይሰጠን›› የሚል ጥያቄ ከመነሳቱ በፊት መንግሥት ከእንጭጩ ሊገታው ይገባልም ብለዋል፡፡
የምረቃውም ታዳሚዎች ይህ ዓይነቱን እኩይና ትውልድ ገዳይ የሆነውን ድርጊት ለመግታት የበኩላቸውን አስተዋጽኦ እንደሚያደርጉ የተናገሩ ሲሆን፤ ከታዳሚዎቹም መካከል አርቲስት ተስፋዬ አበበ ግብረ ሰዶማዊነትን ለመግታት የሚያስችል በአዲስ አበባ ደረጃ አንድ ኮሚቴ እንዲቋቋም ጠይቀው፣ ለኮሚቴውም ሥራ ስኬታማነት ቀስቃሽና ትምህርት አዘል መልዕክት ያላቸውን ልዩ ልዩ መዝሙሮች ለማዘጋጀት ቃል ገብተዋል፡፡ ethiopianreporter.com
ምን ልበልህ በብዙ ነገር ልቤ ቀጥ ሊል ነው (ጌ) ማለት የምድር ተምች ማለት መሆኑን በምን መልኩ እንደማስረዳህ አላውቅም ወላጆች ማስተማር ፣ ማብላት ፣ ማጠጣት ብቻ በቄ ባልሆነበት ዘመን ማድረግ የሚሻለው ጉልበት ይዞ መጮህ ብቻ ነህ የሚያዋጠው እኔ ሌላ ኮመንት ለመስጠት አቅም የለኝም ግን ትውልዱን ሁሉ እግዜያብሔር እንዲባርከው እንለምንም ይሄነው ይሄቢሆን ይሄ አይሆንም ነበር በማለት በከንቱ ግዜያቸውን አንብላባቸው እግዜአብሔር በፈቀደ መጠን ሁሉም ህብረተሰብ የወደለ ያልወለደ ሆዳችንን አንድ አድርገን ብንጮህ ይሄንን አይደለም ሌላም ቀንበር እንሰብር ነበር ምን ያረጋል የኛም በነገሮች አንድ አለመሆን የሚመጣብን ጣጣ ሁሉ የመሸከም አቅም አለመኖር ለነዚህ ችግሮች ያቀርቡናል እስኪ እግዚአብሔር በመፈቀደው ነገር ውስጥ ሁሉ እንዲያልñ ባርከን ብንልካቸው አደለም ከሚወራው ከተወረወረው ነው የሚያወጣቸው ግን ይሄንን አቅም ለኛም የሠራዊት ጌታ ይርዳን ልጆቻችንን በተባረከ ቦታ እንዲያውሉልን እንለምን እንለምን እንለምን እባካችሁ ይሄንን የምታደነቡ ሁሉ አደራ ከዚህ ነገር ተጠበቁ ፡፡
Deleteእግዚአብሔር ማስተዋሉንና መልካሙን ነገር ያምጣልን እንጂ ምን ማድረግ ይቻላል!!!
ReplyDeleteበጣም ያሳዝናል
ReplyDeleteወደ ሕፃናቶቻችን መጡ...የሕብረተሰባችን ዋና ምሰሶዎች የሆኑት ሕፃናቶቻችንና ሴቶቻችን ለዚህ ዲያብሎሳዊ ጥቃት በቅድሚያ እየተጋለጡ እንደሆነ አሁን የምናየው ነው። ለመንፈሳዊ ሕይወታችን ጤንነት እናቶቻችን፣ እህቶቻችን፣ ሴት ልጆቻችን እና ሚስቶቻችን በጣም ከፍተኛ የሆነ ሚና ይጫወታሉ። እግዚአብሔር ማስተዋሉንና መልካሙን ነገር ያምጣልን!but we have to contribute to solveproblem ourselves!
ReplyDeleteyou'r the most brilliant journalist i have ever Known
ReplyDeleteGod bless u God bless Ethiopia
ይህን ከመስማት የበለጠ (ያውም ኢትዮጵያን በመሰለች አገራችን) ለመኖር የሚያስጠላ ነገር የለም። ሌላው ሁሉ ነገር ይቻላል፤ ተችሏልም። ይህ ግን የሚቻል አይደለም። እኔና ቤተሰቤ በምንኖርበት አገር በዚህ ነገር እየተመረርን ስለመጣን ፈጥነን ወደአገራችን ለመግባት አያሰብን ነበር። እዚያም ይህ ነገር መኖሩን ስናነብ የተሰማንን አምላክ ብቻ ነው የሚያውቀው። እስቲ መፍትሔው ላይ አተኩር ዲያቆን።
ReplyDeletethis is what is really going on in this world which is already raised in the bible(paving the way for the false Jesus ) But we have to try to prevent our self, our family and friends & even the society from this immoral doing.
ReplyDeleteDani GOD bless you.
ግደይ ገ/ኪዳን
ReplyDeleteበአገራችን የግብረሰዶማውያን ጥፋት እየበረታ መጥቷል!!በማኅበራዊ ሁኔታቸው ለአጥቂዎች የተጋለጡ ወንዶች ሕፃናት ጉዳቱ ሲደርስባቸው የሚያስታውሳቸውም የለም፡፡ ጥፋተኞቹም በቀላሉ ይታለፋሉ፡፡ ግብረሰዶማውያንን የሚገልጹ ሦስት ወሳኝ ቃላት ናቸው፡- ማደንዘዝ --Desensitization፣ ማፈን --Jamming እና መቀየር --Convert ይሏቸዋል፡፡ ክሪክና ማዲሰን እንደጻፉት ከሆነ የቃላት ስያሜን በመቀያየርና በማምታታት እቅዳቸው ውስጥ የተካተቱትን ዘመቻዎች እውን ማድረግ ወሳኝ ነው ይላሉ፡፡
1.በነርሱ ቋንቋ ማደንዘዝ ማለት በተቻለ መጠን ትንሽ ተቃውሞ ሊያሥነሣ በሚችለው ስልት (በፊልም፣ በሙዚቃ፣ በስደተኞች ጥያቄ፣ የብዝኀ ባህል ጥያቄዎች) ጋር እያስታከኩ የግብረሰዶም ፕሮፓጋንዳ መንዛት ማለት ነው፡፡ ዓላማው ሰዎች በቀጥታ ግብረሰዶማዊ ድርጊትን እንዲቀበሉ ሳይሆን በተዘዋዋሪ አርእስቱን በተደጋጋሚ በማቅረብ ችላ እንዲባልና አስፈላጊው ትኩረት @እንዳያገኝ ማድረግ ነው፡፡ ስያሜያቸውም ግብረሰዶም በሚለው ፈንታ ተመሳሳይ ጾታ ግንኙነት (ሆሞሴክሽዋል)፣ ተጎጂ ሰለባ በሚለው ምትክ “ጌይ” (ደስተኛ) እያሉ መጥራታቸው ይህንኑ ያንፀባርቃል፡፡
2.ሁለተኛው ስትራቴጂያቸው ማፈን ነው፡፡ ይህ የዘመቻው ደረጃ ደግሞ የሚያነጣጥረው የግብረሰዶማውያን አውዳሚና እኩይ ተግባር በሚቃወሙት ላይ ሥነልቦናዊ ሽብር ከመፍጠሩ ላይ የሚያተኩር ነው፡፡ በመግለጫው በእርግጥ አክራሪው (የተፈጥሮ ሕግጋት አክባሪው) እንዲያምን ማድረግ አይጠበቅብንም፤ በሒደት ለዘብተኞቹ አክራሪውን እንዲንቁት ይደረጋል፤ ዋናው ነገር በየትኛውም መንገድ ተጽዕኗችን እውነት ሆነ ትክክለኛ አመክንዮ ባይከተልም ድል ማድረግ መቻሉ ነው፤” ይላል፡፡ ለማፈን ዋናው መሣርያ “መቻቻል” የሚለው ዘመቻ ነው፡፡ እዚህ ላይ በተቃራኒ የቆመውን መቻቻል የማያውቅ “Homo hatred” “የተመሳሳይ ጾታ ግንኙነት ጠላት” የሚል ስም ይሰጡታል፡፡ ከሃይማኖት በመነሣት የሚጠላቸውን “ሃይማኖታዊ የተመሳሳይ ጾታ ግንኙነት ጠላት” ይሉታል፡፡ ሌላኛው እንደነሱ የሆነ ግን እንቅስቃሴያቸውን የማይደግፈውን “gay homophobes” ይሉታል፡፡
3.ሦስተኛው የግብረሰዶማውያን ስትራቴጂ መቀየር ነው፡፡ ይህን ቅየራ በማኅበረሰቡ እውን ለማድረግ በተዘዋዋሪ ተጽዕኖ በሚፈጥሩ ነገሮች፣ የሚቃወሙትን በመወንጀልና ተቋማዊ ማኀበራትን በማደራጀት ሲሆን፣ ይህም የመግለጫው ጸሐፊዎች “ተራውን ዜጋ ስሜቱ፣ አእምሮውና ፈቃዱን ባቀድነው መሠረት ሥነልቦናዊ ጥቃት በመፈጸም መቀየርን ማምጣት ይሆናል፡፡ ሚዲያውን በመጠቀም ለማኅበረሰቡ ፕሮፓጋንዳ በመቀለብ የሚከናወን ነው፤” በዚህ የቅየራ ስልት መሠረት “አክራሪው የሚያውቃቸው በሙሉ በተለይ ግብረሰዶማዊ ከሆኑት ጋር ጥሩ ግንኙነት እንዲመሠርቱ በማድረግ ማሳየት” ይህ ተፈጥሯዊ ሕግ ጠብቆ የሚሔደው ሰው ለዘብተኛ አቋም እንዲኖረው ለማድረግ ነው፡፡http://antiglobalconspiracy.blogspot.com/
Oh, the almighty God protect our country and its people!It is really unbearable to have a 12 year old child being a gay!
ReplyDeleteI would like to ask the mother how she has been treating him and advising him. How about the films he is watching?
F.G
Dessie
Some people are smart like you Daniel, but the second they think they know all, they know nothing. You know nothing about homosexuality, you have no idea how much many of us, Ethiopian Gays are trying to go str8 &/or alter ourselves, to hide our sexuality from our loved ones, just coz they love us to much that, we think knowing our God given sexuality would be seen as something “ill behaving” unfortunately, as you too do see it & thinking that coming out to them will only hurt them, but inspire of, our, life long struggle we never managed to fight nature & God! If that boy wasn't gay, with his parent social class as I have learned from your narration, no one, I believe no one could have the power to influence hem, a boy who could see his mom’s easy & tell her that he is Gay can tell her anything, anything to her, Daniel, to know & feel this you need to be Gay, & I am glad that you are not, I have been teaching in one of the expensive schools in Ethiopia, & I know a boy being out casted & discriminated because of his sexuality, & what is ill is that labeling parents who love their child to much & kiss them in public as abusing their own child, Daniel, what you did not realize is that parents whom really abusing (sexually) their children, I don’t think any Ethiopian parent will do such a thing, would never give you a clue to suspect by kissing their child in public. Let me advice from my experience as a teacher in one of the “best” school in the country, Daniel, what you shall be criticizing should be the level of respect our Amharic language hase in such schools & the ill act by girls & boys! Can I ask which assessment of yours reveled that, Ethiopian gays were drug addicted? If I were you I would have told that mother that……………… "SHE WILL NEVER LOSE HERE SON JUST COZ, HE IS AS GOD MADE HEM TO BE!" WHETHER GAY OR NOT SHE WILL BE HES MOM & GOD WILL BE HIS GOD!" & my other advice to the mother should be to make her see the movie "Prayer to Bobby" which is based on a true story.... hope that mother only needed the best for her son & being gay wasn't such a thing that an Ethiopian Mother want for her child & to be proud of, so she went to you, Mr. Daniel, looking for some help & to that "Dr." unfortunately you both should have been the last people she could go for advice & you were so hateful that you could only had to give what you said.... what a shame....
ReplyDelete"God will alter no gay, coz, there is nothing to alter, as he created all of as we are"
Yard
Dont foolish yourself. You became homosexual (sodome) because you have either been exposed or being victim when you were a child; or else...you have chosen it yourself to be so. How comes you have the moral to advise us here. You are God's creature, as good as any other creatures. Ask yourself, you had a chance to convert and act naturally as straight as you are created to be (even after you became victimized). But rather you denied it. You just go to quench your crazy sexual desire....and finally, you are who you are now. Can you see yourself? you are just trying to promote it here. Do you think after watching movies full of gay agenda we will be more tolerant to homosexuality? Have you ever thought about the natural imbalance you are causing to this world? Nature has its own rules and norms. When any of the rules and norms are violated, there is always a crisis...call it global warming, resource degradation, starvation. The effect of homosexuality is even worse. It is embarrassing! We hate the act of being "homosexual" not you as a person. But if you try to convince us as it is normal or try to promote it, we do not allow that. Let me be so naive and believe you become homosexual (Sodome) by nature, why dont you therapy it? Why dont you medicate it? Why dont you rehabilitate? Rather what you do is, you want to be accepted as normal, you want to celebrate it even. If you cant heal it...just live with it, do not spread your disease.
DeleteBelieve it or not homosexuality will not be accepted as a human right in Ethiopia...it will always be a human vise. Have it on me, it will never see the light of legality in Ethiopia.
Woldesilase
አለምን አንድ ስለማድረግ ሲባል መንግሰት የተቀበለውን ስምምነት ብሰማማም ግን ብትቃራኒው ይዞት የመጣውን ህገወጥ ተግባር እቃወማልሁ. ግን ምን ያደርጋል ኢትዮጲያ ወስጥ ግለሰብ እነጂ ሕዝብ የለምና በማይመለከተኝ ጉዳይ ባልገባ……..አለምን አንድ ስለማድረግ ሲባል መንግሰት የተቀበለውን ስምምነት ብሰማማም ግን ብትቃራኒው ይዞት የመጣውን ህገወጥ ተግባር እቃወማልሁ ግን ምን ያደርጋል ኢትዮጲያ ወስጥ ግለሰብ እነጂ ሕዝብ የለምና በማይመለከተኝ ጉዳይ ባልገባ……..
ReplyDeleteDn Daniel,
ReplyDeleteI told you such things could hardly be fruitful discussing on public media. Perhaps a man named Giday G/Kidan indicated how things are designed for public acceptance. Most of us (may be non of us in this forum) don't at all understand the secret of spirit. Only very few people can understand that. Let's first try to know God. Then we can understand every secret! We here are talking the most easy flesh thoughts. Most of us are just talking our emotion. Look how much we are distant each other in thoughts. But realty on some thing is only one. Please don't post such a thing to public. I told you it might have back fire effect! people may think that what they think is right. They little understand that they mind changes with situations. Hence their truths are with situations not with realities though the actual truth is only one. Please please this issue demands deep and very settled minds! Some body above tried to advice people in a problem to visit Memehir Girma Wondimu. Yes, I also advice every body to listen his taught on secrets of evil spirit. He is the one who unveiled centuries years old hidden realities. Thanks to God! Let's first get the knowledge and power then we can understand how we are being driven.
awey edachin......egnas be Egziabher erdata yefelegnibet heden kezemed kegorebet betim adiren endashan adegin .......endih kifu zeroch sibezu egna lij siniwelid endet linasadigachew yihon.....???
ReplyDeletekemir bettam new yazenkut beteley degifew lemikerakerut
THESE PEOPLE ARE GETTING HELP FROM AGI SO THOSE WHO DELIVER THIS KIND OF ACTIVETY TO MAKE THE PEOPLE UNHUMAN ,THAT WAY THEY CAN EASILY CONTROL THE WHOLE GENERATION .IF SOME ONE LOSS HIS OR HER IDENTITY IN DIFFERENT WAYS,HE OR SHE WON'T GIVE A VALUE FOR ANYTHING ELSE LIKE RELIGION ,HISTORY, CULTURE,NOW A DAYS THE WESTERN AND THE EUROPIAN ARE CHANGING THEIR GAME TO ATTACK AFRICAN ... PLEASE WATCH THIS:-"LIBERIAN PRESEDENT WITH TONY BLAIR ON YOUTUBE".
ReplyDeleteThanks dani for raising such a burning issue,ይህ ችግር ከ ቅርብ ጊዜ ወዲህ በከፍተኛ ደረጃ እየሰፋ ነው እኔ ባካባቢዬ የሚኖሩ 3 እድሜያቸው በወጣትነት የሚገኙ ልጆች አቃለሁ በጣም የሚያሳዝንና የሚያስፈራ ጊዜ ላይ ነን ሁላችንም ህብረተሰቡን ለማንቃት ብዙ መስራት አለብን
ReplyDeleteEvery family has great responsibility to bother about their kids in their day to day activities.
ReplyDeleteLet us pray together.
Bless u Dn.Dani.
Abetu beqa belen. kezih tiwlid geday dirgit ante bechernetih tebiqen. Tizazatihinim yemintebiq enihon zend erdan. amen.
ReplyDeleteamlake hoye yemenaderegewene anawekimina bemaweki weyem balemaweki yeseranewen hateyate yekir belen
ReplyDelete'
Lenesu yemiysfledew mote becha new enesu behebuee tederajetew dergetune endmefesemute hula egname behebue wedmaymlsubet enshgnachewalen yabeden wesha meftehawe megdel becha new.mot le gay enesu eyalu Etihopia weste menem bereket aynoreme.
ReplyDeleteዳኒ እግዚአብሔር ይስጥልን፡፡ አይደፈሬውን አጀንዳ በማንሳትህ
ReplyDeleteይህንን ጉዳይ ካነሳህ ጀምሮ በየቀኑ የሚሰጡትን አስተያየቶች ሳነባቸው የበለጠ እየተጨ ነኩ ነው ጭ ንቅላቴ ሊማፈነዳ ደርሷል፡፡
የ12 ዓመት ወንድ ልጅ አለኝ ግን በምን መልክ እንደምነግረው በጣም ተጨንቄያለሁ፡
ዳኒ እባክህን ለልጆ በሚመጥን መልኩ ሊያነቡት የሚችሉት ነገር ብትጽፍና ወስደን ብናስነብባቸውና ጉዳዩን አብረን ለመወያየት መስመሩን እንዳከፍትልን ብታደርግልን
አምላከ እስራኤል ከዚህ መዓት ይጠብቀን
It has been almost month since i have seen this but couldn't get it out of my mind Daniel I would like to thank you for teaching me in your views but am so scared .where the hell is the world going ? may God protect us from all the evel ideas of davel.
ReplyDeleteዳኒ ምነው ዝም አልክ ጉዳይ ሁለት ቀጥል እንጂ
ReplyDeleteምነው መገናኛ ብዙሃኖቻችን ከማስታወቂያ እና ከአይረቤ የወሬ ሰአታቸው ትንሽ ቀንሰው ለእንደዚህ አይነት ቁም ነገር ቢያውሉት ወይም ለዳኒ አይነት ሰው የአየር ሰአት ቢሰጡ ምን አለበት
ReplyDeleteendezi madiregu yebase semetu bewistachew yalutin lijoch wed ezi hiwot endigebu yadergal..ene ye 19 amt temari negn bezi life west nw yalehute..manem wed ezi hiwot asgebitogn adelem..fikern be sew lib wist yemiyasadir egiziyabher new..ene felge adelem ye wend fiker yeyazegn..yehe neger more of natural nw..zare be addis abeba wist kene edme betache yalu betam bizu lijoch alu..yehen yahl mechenek yalebin aymeslegnem..zare gebresodomawinet adelem ethiopian liyasasibal yemigebaw..bizu rehab ena chigeroch alubat..enezan binefetachew yeshalal..wend ena wend tefaker ena ye geleseboch guday nw..zare be ethiopia sefi hizb alat..ye zere yemeketel chiger yelebatim..yehe yemiyasasib kehon..anyways lib yistachu nw mibalew..manm feligo yemiyarg yelem..weym zemenawint adelm..
Deleteበጣም ቆንጆ ነገር ነው ያነሳኸው ዲ/ዳንኤል እግዚአብሄር ይባርክህ። በመሰረቱ የሰው ልጅን ከሚፈታተኑና ለማመን በሚቸግር ሁኔታ(ህጋዊ መሆኑ በሰው ልጅ ታሪክ) ከሚገኙ ነገሮች አንዱ ግብረሰዶማዊነት ነው። አንዲቷ ቤተ ክርስቲያን ለሁለት ከተሰነጠቀች በኋላ ውስጥ ልውስጥ ሥር ሰዶ ዛሬ ላይ በነጻነት ስም እየተስፋፋ ያለ መርዝ ቢባል ይቀላል። ምስጋና ይግባቸው ላባቶቻችን ጥሩ ስም ሰጥተውታል ግብሩን ቁልጭ አድርጎ ሚያሳይ። እና ሃገራችን ደግሞ ከሌላው ዓለም ባለመለየቷ ይህ መዘዝ በጇ መንኳኳት ጀምሯል። ወደኋላ ትንሽ ልመልሳችሁና ዛሬ ሁሉም በተለከፉ ዜጎቻቸው ምክንያት በሚፈጥሩባቸው ጫና ህጉን እየፈቀዱ ናቸው። ኒውዝላንድ ባለፈው ወር ፈቅዳ ከመላ ዓለም የሚመጡ ጌዮች በይፋ ጋብቻቸውን ይፈጽማሉ።
ReplyDeleteእየንዳንዱ ምዕራባዊ ሃገር ይፋ አለመፍቀዱ እንጂ መብታቸው እንደሆነ፡ በተፍጥሮ ችግር እንዳለባቸው፡ ስባዊ መብታቸው መጠበቅ እንዳለበት ....በሚል አባዜ ባብዛኛው ህሊና በጎ እንደሆነ ይታሰባል። ህጋዊ ለማድረግ ከከበዳችው ዋና ነገር ቅጥሎ በሚመጣ የልጅ ጥያቄ በኩል ነው እንግዲህ መውለድ ስለማይችሉ ለማሳደግ/ባማደጎ/ ቢፈቀድላቸው አስቡት የልጁን እጣ መቼም ከሁለት ጌይ መሃል አድጎ ጤናማ ግለሰብ ይሆናል ፡ አንስት ያገባል ማለት ያልዘሩትን መፈለግ አይነት አይመስልም? ለዚህ ብቻ ነው ሁሌ በየፓርላሜንታቸው ይፈቀድ አይፈቀድ ሚያነታርካቸው መብታቸው እንደሆነማ "ኖርማል" ነው ይሏችኋል። ኢትዮጵያ ከዚህ መቅሰፍት ለዘመናት በሃይማኖት ጋሻ ተከብባ ነበር ዛሬ ግን የምተፈተንበት ሰአት ደረሰ። እንንቃ ጎበዝ ዘመኑ ካበቃለት መቼም ከርሟል ። አስታውሳለሁ በፈረንሳይ የዛሬ 3 ውይም 4 ወር ገደማ ጌይ መሆን በህግ እንደሚፈቀድ ሊታወጅ ቤተ ክርስቲያንም ልታጋባ ስትፈቅድ አንድ ጀግና የሰበካው አዛውንት ይህንን በቁሜ አላይም ብሎ በገዛ ሽጉጡ ደጀሰላሙ ደፍ ላይ ራሱን አጥፍቷል ። አባባሌ ራስን ማጥፋት መደገፌ እንዳይመስል ግን አባቶች ለምነታቸው ምን ያህል እንደሚንገበገቡ ለማለት ነው። እኛም ጋ ገና ማቆጥቆጡ ነውና ካሁኑ ወንድሞችና እህቶች ከላይ በሰፊው እንደተነተኑት በቤተ ክርስቲያን በመገኘት ቃለ እግዚአብሄር መስማት እንደሚያሰፈልግ ማሳሰብ ይገባል። በተለይ በዚህ ዘመን ያለን ክርስቲያኖች ብዙ ሃላፊነት አለብን ያለብንን ተራ ቁርሾዎች ወደጎን በመተው ለበጎ ነገር መስማማት መቻል አለብን። በተልይ ውጭ ያለን ኢትዮጵያውያን በሲኖዶስ ጉዳይ አንዱን ቤተ ክርስቲያን ካንዱ እየለያየን እላይ ታች ስልን በመሃል ልጆቻቸን መሰረታቸውን እስከናካቴ ይስታሉና በጥልቀት እንድናስብበት መጠቆም እወዳለሁ።
Gizew betam yasferal rotew ayameltut tedebkew ayasalfut.geta hoye sewren.enien yeblet yemiyasferan yalew "beshta new"tekbelut belew yemimagetuu sewochn yexafutn saneb new..weyo
ReplyDeleteIt's very sensitive.may God help us.
ReplyDelete‹‹ሙሉ በሙሉ ከችግሩ ወጥቷል ማለት አልችልም፤ አሁንም እጠራጠራለሁ፡፡ ፍርሃቱ ገና አልለቀቀኝም፡፡ ነገር 'ግን ክትትሌን አላቆምኩም፤ ከልጄ ጋር ያለኝን ቀረቤታም ጨምሬያለሁ፤ ስለ ብዙ ነገሮችም እንነጋገራለን፤ የሃይማኖት ትምህርት እንዲማርም እያደረግኩ ነው፡፡ አንድ የማውቀው የሥነ ልቡና ባለሞያ ስለ ግረ ሰዶም ጉዳት በሚገባ ነግሮታል፡፡' I can only say this to this poor mother.............................. "A young person's sexual identity doesn't itself cause them to feel depressed or suicidal. It is the experience of growing up 'different' in a society that often doesn't support difference & is homophobic that can be devastating. The result of this can be what is know as 'internalised homophobia', that is, a person's belief that their sexuality is inferior. Without acceptance, reassurance & support, 'IH' may result in a person trying to hide their sexuality, feeling a sense of shame or engaging in behaviours harmful to self or others" Parent & Family Lesbian & Gay
ReplyDelete