ከአማራ ተረቶች አንዱ እንዲህ ይላል፡፡
የፍየል እና የነብር ግልገሎች በአንድ ሜዳ ላይ አብረው ሲጫወቱ ዋሉ፡፡ ማታ ሁለቱም ወደ የቤታቸው ገቡና ለእናቶቻቸው ውሏቸውን ነገሯቸው፡፡ «እማየ» አለ የነብር ግልገል፡፡ «ዛሬ ወደ ኋላ የተቆለመመ ቀንድ ካለው፡፡ ከኋላው ላይ በቆዳ የተሸፈነ ሥጋ ነገር ከተንጠለጠለበት፤ ሲጮኽ ሚእእእእእእ ከሚል ግልገል ጋር ስጫወት ዋልኩ፡፡ እንዴት ጨዋታ ዐዋቂ መሰለሽ»፡፡