click here for pdf
ከሰሞኑ ሀገራችን አንድ ዓለም አቀፍ ጉባኤ ለማዘጋጀት ሽር ጉድ በማለት ላይ ትገኛለች፡፡ አሥራ ስድስተኛውን የአይካሳ ዓለም ዐቀፍ ጉባኤ፡፡ ሀገሪቱ እንዲህ ያሉ ዓለም ዐቀፍ ጉባኤያትን ማዘጋጀቷ ብዙ ጥቅሞች አሉት፡፡ መልካም ገጽታዋን ለማስተዋወቅ፣ በጉባኤ ቱሪዝም የሚገኘው ገቢ፣ ከሚመጡ ባለሞያዎች ጋር የሚኖረው የዕውቀት ልውውጥ፣ የሚፈጠረው የገበያ እና የሥራ ዕድል፣ ሌሎችም፡፡
ከሰሞኑ ሀገራችን አንድ ዓለም አቀፍ ጉባኤ ለማዘጋጀት ሽር ጉድ በማለት ላይ ትገኛለች፡፡ አሥራ ስድስተኛውን የአይካሳ ዓለም ዐቀፍ ጉባኤ፡፡ ሀገሪቱ እንዲህ ያሉ ዓለም ዐቀፍ ጉባኤያትን ማዘጋጀቷ ብዙ ጥቅሞች አሉት፡፡ መልካም ገጽታዋን ለማስተዋወቅ፣ በጉባኤ ቱሪዝም የሚገኘው ገቢ፣ ከሚመጡ ባለሞያዎች ጋር የሚኖረው የዕውቀት ልውውጥ፣ የሚፈጠረው የገበያ እና የሥራ ዕድል፣ ሌሎችም፡፡
በተቃራኒው ደግሞ ይህንን መሰል ጉባኤያት የሚያስከትሉት አሉታዊ ነገርም አለ፡፡ ቅርሶች ወደ ውጭ የሚወጡበትን መንገድ በመክፈት፣ ባህልን በማበላሸት፣ ዝሙት አዳሪነትን እና ቁማርን በማስፋፋት፣ ለትውልድ እና ሀገር መበላሸት ክፉ አስተዋጽዖም ያደርጋሉ፡፡