ታሪክ ራሱን ይደግማል ይባላል፡፡ በቅዱሳት መጻሕፍት የተጻፉ ምሳሌዎች በአንድ ወቅት ብቻ ተፈጽመው የቀሩ ታሪኮች አይደሉም፡፡ በቤተ ክርስቲያን ታሪክ ውስጥ በየዘመናቱ የሚከሰቱ የቤተ ክርስቲያን ጉዞ አካላት ናቸው፡፡ እነዚህ ለክፉም ሆነ ለበጎ ምሳሌ ሆነው የተጻፉ ታሪኮች፣ ቤተ ክርስቲያንን የመከራ እና የደስታ ዘመናት ተከትለው ይፈጸማሉ፡፡ የዮሐንስ ራእይን ለመተርጎም ከተጻፉ ከግሪክ እና ሶርያ የጥንታውያን መዛግብት ያገኘሁትን ይህንን ትርጓሜ እስኪ ተመልከቱት፡፡
ነገር ግን አንተን የምነቅፍበት ነገር አለኝ፡፡ ሳትሆን ራስዋን ነቢይት ነኝ የምትለውን አገልጋዮቼንም ለጣዖት የተሠዋውን እንዲበሉ እና እንዲሴስኑ የምታስተምረውንና የምታስተውን ያችን ሴት ኤልዛቤልን ዝም ብለሃታልና (ራእይ 2÷20)
ኤልዛቤል ማናት?